መዝሙር 20 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 20:1-9

መዝሙር 20

ጸሎት ለንጉሡ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር በጭንቅ ቀን ይስማህ፤

የያዕቆብም አምላክ ስም ይጠብቅህ።

2ከመቅደሱ ረድኤት ይላክልህ፤

ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ።

3ቍርባንህን ሁሉ ያስብልህ፤

የሚቃጠል መሥዋዕትህን ይቀበልልህ። ሴላ

4የልብህን መሻት ይስጥህ፤

ዕቅድህን ሁሉ ያከናውንልህ።

5በአንተ ድል ደስ ይበለን፤

በአምላካችን ስም አርማችንን ከፍ እናደርጋለን፤

እግዚአብሔር የለመንኸውን ሁሉ ይፈጽምልህ።

6እግዚአብሔር፣ የቀባውን እንደሚያድን

አሁን ዐወቅሁ፤

የማዳን ኀይል ባለው ቀኝ እጁ፣

ከተቀደሰው ሰማይ ይመልስለታል።

7እነዚህ በሰረገላ፣ እነዚያ በፈረስ ይመካሉ፤

እኛ ግን ትምክሕታችን የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም ነው።

8እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ፤

እኛ ግን ተነሣን፤ ጸንተንም ቆምን።

9እግዚአብሔር ሆይ፤ ንጉሥን አድን፤

እኛም በጠራንህ ቀን ስማን።20፥9 ወይም አድን! ንጉሥ ሆይ፤ ስማን

Ketab El Hayat

مزمور 20:1-9

الْمَزْمُورُ الْعِشْرُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1لِيَسْتَجِبْ لَكَ الرَّبُّ فِي يَوْمِ ضِيقِكَ. لِيَحْرُسْكَ اسْمُ إِلَهِ يَعْقُوبَ. 2لِيُرْسِلْ لَكَ عَوْناً مِنْ مَقْدِسِهِ، وَمُسَانَدَةً مِنْ صِهْيَوْنَ. 3لِيَتَذَكَّرْ جَمِيعَ تَقْدِمَاتِكَ، وَيَتَقَبَّلْ مُحْرَقَاتِكَ. 4لِيُعْطِكَ بُغْيَةَ قَلْبِكَ، وَيُتَمِّمْ لَكَ كُلَّ مَقَاصِدِكَ. 5نَهْتِفُ مُبْتَهِجِينَ بِخَلاصِكَ، وَبِاسْمِ إِلَهِنَا نَرْفَعُ رَايَتَنَا، لِيُحَقِّقْ لَكَ الرَّبُّ كُلَّ مَا تَسْأَلُهُ.

6الآنَ أَدْرَكْتُ أَنَّ الرَّبَّ يُخَلِّصُ مَسِيحَهُ، وَيَسْتَجِيبُ مِنْ سَمَاوَاتِهِ الْمُقَدَّسَةِ، بِقُدْرَةِ يَمِينِهِ الْمُخَلِّصَةِ. 7يَتَّكِلُ هَؤُلاءِ عَلَى مَرْكَبَاتِ الْحَرْبِ، وَأُولَئِكَ عَلَى الْخَيْلِ. أَمَّا نَحْنُ فَنَتَّكِلُ عَلَى اسْمِ الرَّبِّ إِلَهِنَا. 8هُمْ خَرُّوا وَسَقَطُوا، أَمَّا نَحْنُ فَنَهَضْنَا وَانْتَصَبْنَا. 9خَلِّصْ يَا رَبُّ! لِيَسْتَجِبِ الْمَلِكُ حِينَ نَدْعُوهُ.