መዝሙር 2 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 2:1-12

መዝሙር 2

መሲሓዊ ትዕይንት

1ሕዝቦች ለምን ያሤራሉ?2፥1 ዕብራይስጡ እንዲሁ ሲሆን፣ ሰብዓ ሊቃናት ግን ይቈጣሉ ይላል።

ሰዎችስ ለምን ከንቱ ነገር ያውጠነጥናሉ?

2የምድር ነገሥታት ተነሡ፤

ገዦችም በእግዚአብሔርና በመሲሑ2፥2 ወይም የተቀባው ላይ

ሊመክሩ ተሰበሰቡ፤

3“ሰንሰለታቸውን እንበጥስ፣

የእግር ብረታቸውንም አውልቀን እንጣል” አሉ።

4በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጠው ይሥቃል፤

ጌታም ይሣለቅባቸዋል።

5ከዚያም በቍጣው ይናገራቸዋል፤

በመዓቱም ያስደነግጣቸዋል፤

6ደግሞም፣ “እኔ ግን በተቀደሰው ተራራዬ፣

በጽዮን ላይ የራሴን ንጉሥ ሾምሁ” ይላል።

7የእግዚአብሔርን ሕግ ዐውጃለሁ፤

እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “አንተ ልጄ ነህ፤

እኔ ዛሬ ወለድሁህ፤2፥7 ወይም …አባትህ ሆንሁ

8ለምነኝ፤

መንግሥታትን ርስት አድርጌ፣

የምድርንም ዳርቻ ግዛት እንዲሆንህ እሰጥሃለሁ።

9አንተም በብረት በትር ትቀጠቅጣቸዋለህ፤2፥9 ወይም በብረት ዘንግ ትሰባብራቸዋለህ

እንደ ሸክላ ዕቃ ታደቅቃቸዋለህ።”

10ስለዚህ እናንት ነገሥታት ልብ በሉ፤

እናንት የምድር ገዦችም፣ ተጠንቀቁ።

11እግዚአብሔርን በፍርሀት አገልግሉት፤

ለእርሱ መራድም ደስ ያሰኛችሁ።

12እንዳይቈጣና በመንገድ እንዳትጠፉ፣

ዝቅ ብላችሁ ልጁን ሳሙት፤

ቍጣው ፈጥኖ ይነድዳልና።

እርሱን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ የተባረኩ ናቸው።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 2:1-12

2

1主に向かって怒り狂うとは、

なんと愚かな国々でしょう。

神を出し抜こうとするとは、

なんと身のほど知らずな人々でしょう。

2地上の王たちが相集い、

主と、主に油注がれた者への反逆をもくろんでいます。

3彼らは言います。

「さあ、神の鎖を断ち切ろう。

神から解放されようではないか。」

4天におられる神は、

彼らのむなしい計画を聞いて笑います。

5それから、激しい怒りを燃やしてしかりつけ、

彼らを恐れおののかせます。

6主は言われます。

「これがわたしの選んだ王だ。

わたしは彼を、わたしの聖なる都エルサレムで即位させた。」

7選ばれた方が答えます。

「主の永遠の目的を知らせましょう。

主は私に、『わが子よ、今日はあなたの戴冠式だ。

今、わたしはあなたに、子にふさわしい栄光を与える』

と告げられました。」

8「わたしに願い求めよ。

そうすれば、世界のすべての国を授けよう。

9国々を鉄の杖で治め、

粘土のつぼのように砕くがよい。」

10ああ、この世の王、支配者たちよ。

手遅れにならないうちに聞きなさい。

11敬虔な恐れを抱いて主に仕え、

おののきをもって喜びなさい。

12神のひとり子の前にひれ伏し、

その足に口づけしなさい。

主の怒りにふれて、滅ぼされてしまう前に。

私はあなたに警告しておきます。

主の怒りがまもなく燃え上がろうとしています。

主に信頼する人は、なんと幸いでしょう。