መዝሙር 2 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 2:1-12

መዝሙር 2

መሲሓዊ ትዕይንት

1ሕዝቦች ለምን ያሤራሉ?2፥1 ዕብራይስጡ እንዲሁ ሲሆን፣ ሰብዓ ሊቃናት ግን ይቈጣሉ ይላል።

ሰዎችስ ለምን ከንቱ ነገር ያውጠነጥናሉ?

2የምድር ነገሥታት ተነሡ፤

ገዦችም በእግዚአብሔርና በመሲሑ2፥2 ወይም የተቀባው ላይ

ሊመክሩ ተሰበሰቡ፤

3“ሰንሰለታቸውን እንበጥስ፣

የእግር ብረታቸውንም አውልቀን እንጣል” አሉ።

4በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጠው ይሥቃል፤

ጌታም ይሣለቅባቸዋል።

5ከዚያም በቍጣው ይናገራቸዋል፤

በመዓቱም ያስደነግጣቸዋል፤

6ደግሞም፣ “እኔ ግን በተቀደሰው ተራራዬ፣

በጽዮን ላይ የራሴን ንጉሥ ሾምሁ” ይላል።

7የእግዚአብሔርን ሕግ ዐውጃለሁ፤

እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “አንተ ልጄ ነህ፤

እኔ ዛሬ ወለድሁህ፤2፥7 ወይም …አባትህ ሆንሁ

8ለምነኝ፤

መንግሥታትን ርስት አድርጌ፣

የምድርንም ዳርቻ ግዛት እንዲሆንህ እሰጥሃለሁ።

9አንተም በብረት በትር ትቀጠቅጣቸዋለህ፤2፥9 ወይም በብረት ዘንግ ትሰባብራቸዋለህ

እንደ ሸክላ ዕቃ ታደቅቃቸዋለህ።”

10ስለዚህ እናንት ነገሥታት ልብ በሉ፤

እናንት የምድር ገዦችም፣ ተጠንቀቁ።

11እግዚአብሔርን በፍርሀት አገልግሉት፤

ለእርሱ መራድም ደስ ያሰኛችሁ።

12እንዳይቈጣና በመንገድ እንዳትጠፉ፣

ዝቅ ብላችሁ ልጁን ሳሙት፤

ቍጣው ፈጥኖ ይነድዳልና።

እርሱን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ የተባረኩ ናቸው።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 2:1-12

第 2 篇

上帝膏立的君王

1列国为何咆哮?

万民为何枉费心机?

2世上的君王一同行动,

官长聚集商议,

要抵挡耶和华和祂所膏立的王。

3他们说:

“让我们挣断他们的锁链,

脱去他们的捆索!”

4坐在天上宝座上的主必笑他们,

祂必嘲笑他们。

5那时,祂必怒斥他们,

使他们充满恐惧。

6祂说:

“在我的锡安圣山上,

我已立了我的君王。”

7那位君王说:

“我要宣告耶和华的旨意,

祂对我说,‘你是我的儿子,

我今日成为你父亲。

8你向我祈求,我必把列国赐给你作产业,

让天下都归你所有。

9你要用铁杖统治他们,

把他们像陶器一般打碎。’”

10君王啊,要慎思明辨!

世上的统治者啊,要接受劝诫!

11要以敬畏的心事奉耶和华,

要喜乐也要战战兢兢。

12要降服在祂儿子面前,

免得祂发怒,

你们便在罪恶中灭亡,

因为祂的怒气将临。

投靠祂的人有福了!