መዝሙር 19 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 19:1-14

መዝሙር 19

እግዚአብሔር የጽድቅ ፀሓይ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤

የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያውጃሉ።

2ቀን ለሌላው ቀን ይናገራል፤

ሌሊትም ለሌሊት ዕውቀትን ይገልጣል፤

3ንግግር የለም፤ ቃል የለም፤

ድምፃቸው በጆሮ የሚሰማ አይደለም።19፥3 ወይም የሚናገሩት የላቸውም፤ ቃላት የለም፤ ከእርሱ ምንም ድምፅ አይሰማም

4ያም ሆኖ ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፣

ቃላቸውም19፥4 ሰብዓ ሊቃናት የሩምና ሱርስት እንዲሁ ሲሆኑ፣ ዕብራይስጡ ግን ድንበራቸው ይላል። እስከ ዓለም ዳርቻ ይወጣል።

እርሱ በሰማያት ለፀሓይ ድንኳን ተክሏል፤

5ፀሓይም ከእልፍኙ እንደሚወጣ ሙሽራ ይወጣል፤

ወደ ግቡም እንደሚሮጥ ብርቱ ሰው ደስ ይለዋል።

6መውጫው ከሰማያት ዳርቻ ነው፤

ዑደቱም እስከ ሌላኛው ዳርቻ ነው፤

ከትኵሳቱም የሚሰወር የለም።

7የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤

ነፍስንም መልሶ ያለመልማል፤

የእግዚአብሔር ሥርዐት የታመነ ነው፤

አላዋቂውን ጥበበኛ ያደርጋል።

8የእግዚአብሔር ሕግጋት ትክክል ናቸው፤

ልብን ደስ ያሰኛሉ።

የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፤

ዐይንን ያበራል።

9እግዚአብሔርን መፍራት ንጹሕ ነው፤

ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

የእግዚአብሔር ፍርድ የታመነ፣

ሁለንተናውም ጻድቅ ነው፤

10ከወርቅ ይልቅ የከበረ፣

እጅግ ከጠራ ወርቅም የተሻለ ነው፤

ከማር ይልቅ ይጣፍጣል፤

ከማር ወለላም ይበልጥ ይጥማል።

11ደግሞም አገልጋይህ በእርሱ ጥንቃቄ ያደርጋል፤

እርሱንም መጠበቅ ወሮታ አለው።

12ስሕተቱን ማን ሊያስተውል ይችላል?

ከተሰወረ በደል አንጻኝ።

13ባሪያህን ከድፍረት ኀጢአት ጠብቅ፤

እንዳይሠለጥንብኝም ርዳኝ፤

ያን ጊዜ ያለ እንከን እሆናለሁ፤

ከታላቅ በደልም እነጻለሁ።

14መጠጊያዬና አዳኜ እግዚአብሔር ሆይ፤

የአፌ ቃልና የልቤ ሐሳብ፣

በፊትህ ያማረ ይሁን።

Persian Contemporary Bible

مزامير 19:1-14

عظمت خدا در خلقت

1آسمان از شكوه و عظمت خدا حكايت می‌كند و صنعت دستهای او را نشان می‌دهد. 2روز و شب حكمت خدا را اعلام می‌نمايند؛ 3‏-4و بی‌آنكه سخنی بگويند، ساكت و خاموش پيام خود را به سراسر جهان می‌رسانند. 5آفتاب هر صبح از خانه‌ای كه خدا برايش در آسمان قرار داده است مانند تازه دامادی خوشحال و مانند قهرمانی كه مشتاقانه منتظر دويدن در ميدان است، بيرون می‌آيد. 6از يک سوی آسمان به سوی ديگر می‌شتابد، و حرارتش همه جا را فرا می‌گيرد.

احكام خداوند

7احكام خداوند كامل است و جان را تازه می‌سازد، كلام خداوند قابل اعتماد است و به ساده‌دلان حكمت می‌بخشد. 8فرامين خداوند راست است و دل را شاد می‌سازد، اوامر خداوند پاک است و بصيرت می‌بخشد. 9قوانين خداوند قابل احترام و نيكوست و تا ابد برقرار می‌ماند. احكام خداوند تماماً حق و عدل است، 10از طلای ناب مرغوبتر و از عسل خالص شيرينتر. 11احكام تو بنده‌ات را آگاه و هوشيار می‌سازد و هر كه آنها را بجا آورد، پاداش عظيمی خواهد يافت.

12كيست كه بتواند به گناهان نهان خود پی ببرد؟ خداوندا، تو مرا از چنين گناهان پاک ساز! 13و نيز مرا از گناهان عمدی بازدار و نگذار بر من مسلط شوند. آنگاه خواهم توانست از شر گناه آزاد شده، بی‌عيب باشم.

14ای خداوند، ای پناهگاه و نجات دهندهٔ من، سخنان و افكارم مورد پسند تو باشند.