መዝሙር 19 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 19:1-14

መዝሙር 19

እግዚአብሔር የጽድቅ ፀሓይ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤

የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያውጃሉ።

2ቀን ለሌላው ቀን ይናገራል፤

ሌሊትም ለሌሊት ዕውቀትን ይገልጣል፤

3ንግግር የለም፤ ቃል የለም፤

ድምፃቸው በጆሮ የሚሰማ አይደለም።19፥3 ወይም የሚናገሩት የላቸውም፤ ቃላት የለም፤ ከእርሱ ምንም ድምፅ አይሰማም

4ያም ሆኖ ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፣

ቃላቸውም19፥4 ሰብዓ ሊቃናት የሩምና ሱርስት እንዲሁ ሲሆኑ፣ ዕብራይስጡ ግን ድንበራቸው ይላል። እስከ ዓለም ዳርቻ ይወጣል።

እርሱ በሰማያት ለፀሓይ ድንኳን ተክሏል፤

5ፀሓይም ከእልፍኙ እንደሚወጣ ሙሽራ ይወጣል፤

ወደ ግቡም እንደሚሮጥ ብርቱ ሰው ደስ ይለዋል።

6መውጫው ከሰማያት ዳርቻ ነው፤

ዑደቱም እስከ ሌላኛው ዳርቻ ነው፤

ከትኵሳቱም የሚሰወር የለም።

7የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤

ነፍስንም መልሶ ያለመልማል፤

የእግዚአብሔር ሥርዐት የታመነ ነው፤

አላዋቂውን ጥበበኛ ያደርጋል።

8የእግዚአብሔር ሕግጋት ትክክል ናቸው፤

ልብን ደስ ያሰኛሉ።

የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፤

ዐይንን ያበራል።

9እግዚአብሔርን መፍራት ንጹሕ ነው፤

ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

የእግዚአብሔር ፍርድ የታመነ፣

ሁለንተናውም ጻድቅ ነው፤

10ከወርቅ ይልቅ የከበረ፣

እጅግ ከጠራ ወርቅም የተሻለ ነው፤

ከማር ይልቅ ይጣፍጣል፤

ከማር ወለላም ይበልጥ ይጥማል።

11ደግሞም አገልጋይህ በእርሱ ጥንቃቄ ያደርጋል፤

እርሱንም መጠበቅ ወሮታ አለው።

12ስሕተቱን ማን ሊያስተውል ይችላል?

ከተሰወረ በደል አንጻኝ።

13ባሪያህን ከድፍረት ኀጢአት ጠብቅ፤

እንዳይሠለጥንብኝም ርዳኝ፤

ያን ጊዜ ያለ እንከን እሆናለሁ፤

ከታላቅ በደልም እነጻለሁ።

14መጠጊያዬና አዳኜ እግዚአብሔር ሆይ፤

የአፌ ቃልና የልቤ ሐሳብ፣

በፊትህ ያማረ ይሁን።

King James Version

Psalms 19:1-14

To the chief Musician, A Psalm of David.

1The heavens declare the glory of God; and the firmament sheweth his handywork.

2Day unto day uttereth speech, and night unto night sheweth knowledge.

3There is no speech nor language, where their voice is not heard.19.3 where…: or, without these their voice is heard: Heb. without their voice heard

4Their line is gone out through all the earth, and their words to the end of the world. In them hath he set a tabernacle for the sun,19.4 line: or, rule, or, direction

5Which is as a bridegroom coming out of his chamber, and rejoiceth as a strong man to run a race.

6His going forth is from the end of the heaven, and his circuit unto the ends of it: and there is nothing hid from the heat thereof.

7The law of the LORD is perfect, converting the soul: the testimony of the LORD is sure, making wise the simple.19.7 law: or, doctrine19.7 converting: or, restoring

8The statutes of the LORD are right, rejoicing the heart: the commandment of the LORD is pure, enlightening the eyes.

9The fear of the LORD is clean, enduring for ever: the judgments of the LORD are true and righteous altogether.19.9 true: Heb. truth

10More to be desired are they than gold, yea, than much fine gold: sweeter also than honey and the honeycomb.19.10 the honeycomb: Heb. the dropping of honeycombs

11Moreover by them is thy servant warned: and in keeping of them there is great reward.

12Who can understand his errors? cleanse thou me from secret faults.

13Keep back thy servant also from presumptuous sins; let them not have dominion over me: then shall I be upright, and I shall be innocent from the great transgression.19.13 the great: or, much

14Let the words of my mouth, and the meditation of my heart, be acceptable in thy sight, O LORD, my strength, and my redeemer.19.14 strength: Heb. rock