መዝሙር 17 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 17:1-15

መዝሙር 17

የንጹሕ ሰው አቤቱታ

የዳዊት ጸሎት።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በቅንነት የቀረበውን አቤቱታዬን ስማ፤

ጩኸቴንም አድምጥ፤

ከአታላይ ከንፈር ያልወጣውን፣

ጸሎቴን አድምጥ።

2ጽድቄ ከአንተ ዘንድ ይምጣ፤

ዐይኖችህም ፍትሕን ይዩ።

3ልቤን መረመርኸው፣ በሌሊት ጠጋ

ብለህ ፈተንኸኝ፤

ፈተሽኸኝ አንዳች አላገኘህብኝም፤

አንደበቴም ዕላፊ አልሄደም።

4ከሰዎች ተግባር፣

በከንፈርህ ቃል፣

ከዐመፀኞች መንገድ፣

ራሴን ጠብቄአለሁ።

5አረማመዴ በመንገድህ ጸንቷል

እግሮቼም አልተንሸራተቱም።

6አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ አንተን እጣራለሁ፤

ጆሮህን ወደ እኔ ጣል አድርገህ ጸሎቴን ስማ።

7ከጠላቶቻቸው መተገኛ ያደረጉህን፣

በቀኝ እጅህ የምትታደግ ሆይ፤

ጽኑ ፍቅርህን ድንቅ አድርገህ ግለጥ።

8እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤

በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤

9ከሚያስጨንቁኝ ከክፉዎች፣

ከሚከብቡኝ አደገኛ ባላንጣዎቼ ጋርደኝ።

10ደንዳና ልባቸውን ደፈኑት፤

በአፋቸውም ትዕቢት ይናገራሉ።

11አሳድደው ደረሱብኝ፤ ከበቡኝም፤

መሬት ላይ ሊዘርሩኝም አፈጠጡብኝ።

12እነርሱ ለንጥቂያ እንደሚጓጓ አንበሳ፣

በስውርም እንደሚያደባ ደቦል አንበሳ ናቸው።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ተነሥተህ ግጠማቸውና ጣላቸው፤

በሰይፍህም ከክፉዎች ታደገኝ።

14እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዲህ ካሉት ሰዎች በክንድህ አድነኝ፤

ዕድል ፈንታቸው ይህችው ሕይወት ብቻ ከሆነች፣ ከዚህ ዓለም ሰዎች ታደገኝ።

ከመዝገብህ ሆዳቸውን ሞላህ፤

ልጆቻቸውም ተትረፍርፎላቸዋል፤

ለልጆቻቸውም ሀብት ያከማቻሉ።

15እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤

ስነቃም ክብርህን አይቼ እረካለሁ።

Ketab El Hayat

مزمور 17:1-15

الْمَزْمُورُ السَّابِعَ عَشَرَ

صَلاةٌ رَفَعَهَا دَاوُدُ

1اسْمَعْ يَا رَبُّ دَعْوَى الْحَقِّ. أَنْصِتْ إِلَى صُرَاخِي، وَأَصْغِ إِلَى صَلاتِي الصَّاعِدَةِ مِنْ شَفَتَيْنِ صَادِقَتَيْنِ. 2لِيَخْرُجْ مِنْ أَمَامِكَ قَضَائِي، وَلْتُلاحِظْ عَيْنَاكَ اسْتِقَامَتِي. 3اخْتَبَرْتَ قَلْبِي إِذِ افْتَقَدْتَنِي لَيْلاً، وَامْتَحَنْتَنِي فَلَمْ تَجِدْ فِيَّ سُوءاً. لَمْ تُخَالِفْ أَقْوَالِي أَفْكَارِي. 4مَا شَأْنِي بِأَعْمَالِ النَّاسِ الشِّرِّيرَةِ؟ فَبِفَضْلِ كَلامِ شَفَتَيْكَ تَفَادَيْتُ مَسَالِكَ الْعَنِيفِ. 5ثَبَّتُّ خُطْوَاتِي فِي طُرُقِكَ فَلَمْ تَزِلَّ قَدَمَايَ.

6إِلَيْكَ دَعَوْتُ اللهُمَّ، لأَنَّكَ تَسْتَجِيبُ، فَأَرهِفْ إِلَيَّ أُذُنَكَ وَأَصْغِ لِكَلامِي. 7أَظْهِرْ رَوْعَةَ مَرَاحِمِكَ يَا مَنْ تُخَلِّصُ بِيَمِينِكَ مَنْ يَلْتَجِئُونَ إِلَيْكَ مِنْ مُطَارِدِيهِمْ. 8احْفَظْنِي كَحَدَقَةِ عَيْنِكَ، وَاسْتُرْنِي بِظِلِّ جَنَاحَيْكَ. 9احْفَظْنِي مِنَ الأَشْرَارِ الَّذِينَ يُخْرِبُونَنِي، مِنْ أَعْدَائِي الْقَتَلَةِ الْمُحْدِقِينَ بِي. 10عَوَاطِفُهُمْ مُتَحَجِّرَةٌ لَا تُشْفِقُ. أَفْوَاهُهُمْ تَنْطِقُ بِالْكِبْرِيَاءِ. 11حَاصَرُونَا مِنْ كُلِّ جِهَةٍ، وَوَطَّدُوا العَزْمَ عَلَى طَرْحِنَا أَرْضاً. 12الشِّرِّيرُ كَأَسَدٍ مُتَلَهِّفٍ لِلاِفْتِرَاسِ، وَكَالشِّبْلِ الْكَامِنِ فِي مَخْبَئِهِ. 13قُمْ يَا رَبُّ تَصَدَّ لَهُ. اصْرَعْهُ. وَبِسَيْفِكَ نَجِّ نَفْسِي مِنَ الشِّرِّيرِ. 14أَنْقِذْنِي بِيَدِكَ يَا رَبُّ مِنَ النَّاسِ. مِنْ أَهْلِ الدُّنْيَا الَّذِينَ نَصِيبُهُمْ هُوَ فِي هَذِهِ الْحَيَاةِ. أَنْتَ تَمْلَأُ بُطُونَهُمْ مِنْ خَيْرَاتِكَ الْمَخْزُونَةِ، فَيَشْبَعُ أَبْنَاؤُهُمْ، وَيُوَرِّثُونَ أَوْلادَهُمْ مَا يَفْضُلُ عَنْهُمْ. 15أَمَّا أَنَا فَبِالْبِرِّ أُشَاهِدُ وَجْهَكَ. أَشْبَعُ، إِذَا اسْتَيْقَظْتُ، مِنْ بَهَاءِ طَلْعَتِكَ.