መዝሙር 17 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 17:1-15

መዝሙር 17

የንጹሕ ሰው አቤቱታ

የዳዊት ጸሎት።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በቅንነት የቀረበውን አቤቱታዬን ስማ፤

ጩኸቴንም አድምጥ፤

ከአታላይ ከንፈር ያልወጣውን፣

ጸሎቴን አድምጥ።

2ጽድቄ ከአንተ ዘንድ ይምጣ፤

ዐይኖችህም ፍትሕን ይዩ።

3ልቤን መረመርኸው፣ በሌሊት ጠጋ

ብለህ ፈተንኸኝ፤

ፈተሽኸኝ አንዳች አላገኘህብኝም፤

አንደበቴም ዕላፊ አልሄደም።

4ከሰዎች ተግባር፣

በከንፈርህ ቃል፣

ከዐመፀኞች መንገድ፣

ራሴን ጠብቄአለሁ።

5አረማመዴ በመንገድህ ጸንቷል

እግሮቼም አልተንሸራተቱም።

6አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ አንተን እጣራለሁ፤

ጆሮህን ወደ እኔ ጣል አድርገህ ጸሎቴን ስማ።

7ከጠላቶቻቸው መተገኛ ያደረጉህን፣

በቀኝ እጅህ የምትታደግ ሆይ፤

ጽኑ ፍቅርህን ድንቅ አድርገህ ግለጥ።

8እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤

በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤

9ከሚያስጨንቁኝ ከክፉዎች፣

ከሚከብቡኝ አደገኛ ባላንጣዎቼ ጋርደኝ።

10ደንዳና ልባቸውን ደፈኑት፤

በአፋቸውም ትዕቢት ይናገራሉ።

11አሳድደው ደረሱብኝ፤ ከበቡኝም፤

መሬት ላይ ሊዘርሩኝም አፈጠጡብኝ።

12እነርሱ ለንጥቂያ እንደሚጓጓ አንበሳ፣

በስውርም እንደሚያደባ ደቦል አንበሳ ናቸው።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ተነሥተህ ግጠማቸውና ጣላቸው፤

በሰይፍህም ከክፉዎች ታደገኝ።

14እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዲህ ካሉት ሰዎች በክንድህ አድነኝ፤

ዕድል ፈንታቸው ይህችው ሕይወት ብቻ ከሆነች፣ ከዚህ ዓለም ሰዎች ታደገኝ።

ከመዝገብህ ሆዳቸውን ሞላህ፤

ልጆቻቸውም ተትረፍርፎላቸዋል፤

ለልጆቻቸውም ሀብት ያከማቻሉ።

15እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤

ስነቃም ክብርህን አይቼ እረካለሁ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 17:1-15

第 17 篇

无辜者的祈祷

大卫的祈祷。

1耶和华啊,

求你听我祈求公义的声音,

侧耳听我的呼求,

垂听我真诚的祷告。

2愿你宣判我无罪,

愿你明察是非。

3你试验过我的心思,

夜间鉴察过我,磨炼过我,

找不出任何过犯;

我立志口不犯罪。

4我遵守你的教导,洁身自守,

不与残暴之徒同流。

5我坚定地走你的道路,

从未偏离。

6上帝啊!我向你祈祷,

因为你必应允我。

求你垂听我的祷告。

7求你彰显你奇妙的慈爱,

用右手拯救投靠你的人脱离仇敌。

8求你保护我,像保护眼中的瞳仁,

用你的翅膀荫庇我,

9救我脱离恶人的攻击,

脱离四围杀气腾腾的仇敌。

10他们良心丧尽,口出狂言。

11他们穷追围堵,

伺机把我打倒在地。

12他们像急于撕碎猎物的饿狮,

又像蹲伏在暗处的猛狮。

13耶和华啊,

求你起来迎头击倒他们,

求你持刀救我脱离恶人。

14耶和华啊,

求你伸手救我脱离这些人,

脱离这些只在今生有福分的世人。

你使他们财宝无数。

他们儿女众多,

还把财富留给子孙。

15但我因持守公义必见你的面;

我醒来见到你就心满意足了。