መዝሙር 150 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 150:1-6

መዝሙር 150

የምስጋና መዝሙር

1ሃሌ ሉያ።150፥1 አንዳንዶች ከ6 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤

በታላቅ ጠፈሩ አወድሱት።

2ስለ ብርቱ ሥራው አመስግኑት፤

እጅግ ታላቅ ነውና ወድሱት።

3በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤

በበገናና በመሰንቆ ወድሱት።

4በከበሮና በሽብሸባ አመስግኑት፤

በባለ አውታር መሣሪያና በእንቢልታ አወድሱት።

5ተርገብጋቢ ድምፅ ባለው ጸናጽል አመስግኑት፤

ድምፀ መልካም በሆነ ጸናጽል ወድሱት።

6እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን።

ሃሌ ሉያ።

Ketab El Hayat

مزمور 150:1-6

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالْخَمْسُونَ

1هَلِّلُويَا! سَبِّحُوا اللهَ فِي هَيْكَلِهِ. سَبِّحُوهُ فِي السَّمَاءِ الَّتِي صَنَعَهَا بِقُدْرَتِهِ 2سَبِّحُوهُ مِنْ أَجْلِ أَعْمَالِهِ الْمُقْتَدِرَةِ. سَبِّحُوهُ حَسَبَ عَظَمَتِهِ الفَائِقَةِ. 3سَبِّحُوهُ بِصَوْتِ بُوقٍ. سَبِّحُوهُ بِالرَّبَابِ وَالْعُودِ. 4سَبِّحُوهُ بِالدُّفِّ وَالرَّقْصِ. سَبِّحُوهُ بِأَوْتَارٍ وَمِزْمَارٍ. 5سَبِّحُوهُ عَلَى وَقْعِ الصُّنُوجِ. سَبِّحُوهُ بالصُّنُوجِ الْمُدَوِّيَّةِ. 6لِتُسَبِّحِ الرَّبَّ كُلُّ نَسَمَةٍ. هَلِّلُويَا.