መዝሙር 149 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 149:1-9

መዝሙር 149

የድል መዝሙር

1ሃሌ ሉያ።149፥1 አንዳንዶች ከ9 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

ለእግዚአብሔር አዲስ ቅኔ ተቀኙ፤

ምስጋናውንም በቅዱሳን ጉባኤ ዘምሩ።

2እስራኤል በፈጣሪው ደስ ይበለው፤

የጽዮንም ልጆች በንጉሣቸው ሐሤት ያድርጉ።

3ስሙን በሽብሸባ ያመስግኑ፤ በከበሮና በመሰንቆ ይዘምሩለት።

4እግዚአብሔር በሕዝቡ ደስ ይለዋልና፤

የዋሃንንም በማዳኑ ውበት ያጐናጽፋል።

5ቅዱሳን በዚህ ክብር ይጓደዱ፤

በመኝታቸውም ላይ እልል እያሉ ይዘምሩ።

6የአምላክ ውዳሴ በአንደበታቸው፣

ባለ ሁለት ልሳን ሰይፍም በእጃቸው ይሁን፤

7በዚህ ሕዝቦችን ይበቀላሉ፤

ሰዎችንም ይቀጣሉ፤

8ነገሥታታቸውን በሰንሰለት፣

መኳንንታቸውንም በእግር ብረት ያስራሉ፤

9ይህም በእነርሱ ላይ የተጻፈውን ፍርድ ለመፈጸም ነው።

ለቅዱሳኑም ሁሉ ይህች ክብር ናት።

ሃሌ ሉያ።

New International Version

Psalms 149:1-9

Psalm 149

1Praise the Lord.149:1 Hebrew Hallelu Yah; also in verse 9

Sing to the Lord a new song,

his praise in the assembly of his faithful people.

2Let Israel rejoice in their Maker;

let the people of Zion be glad in their King.

3Let them praise his name with dancing

and make music to him with timbrel and harp.

4For the Lord takes delight in his people;

he crowns the humble with victory.

5Let his faithful people rejoice in this honor

and sing for joy on their beds.

6May the praise of God be in their mouths

and a double-edged sword in their hands,

7to inflict vengeance on the nations

and punishment on the peoples,

8to bind their kings with fetters,

their nobles with shackles of iron,

9to carry out the sentence written against them—

this is the glory of all his faithful people.

Praise the Lord.