መዝሙር 149 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 149:1-9

መዝሙር 149

የድል መዝሙር

1ሃሌ ሉያ።149፥1 አንዳንዶች ከ9 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

ለእግዚአብሔር አዲስ ቅኔ ተቀኙ፤

ምስጋናውንም በቅዱሳን ጉባኤ ዘምሩ።

2እስራኤል በፈጣሪው ደስ ይበለው፤

የጽዮንም ልጆች በንጉሣቸው ሐሤት ያድርጉ።

3ስሙን በሽብሸባ ያመስግኑ፤ በከበሮና በመሰንቆ ይዘምሩለት።

4እግዚአብሔር በሕዝቡ ደስ ይለዋልና፤

የዋሃንንም በማዳኑ ውበት ያጐናጽፋል።

5ቅዱሳን በዚህ ክብር ይጓደዱ፤

በመኝታቸውም ላይ እልል እያሉ ይዘምሩ።

6የአምላክ ውዳሴ በአንደበታቸው፣

ባለ ሁለት ልሳን ሰይፍም በእጃቸው ይሁን፤

7በዚህ ሕዝቦችን ይበቀላሉ፤

ሰዎችንም ይቀጣሉ፤

8ነገሥታታቸውን በሰንሰለት፣

መኳንንታቸውንም በእግር ብረት ያስራሉ፤

9ይህም በእነርሱ ላይ የተጻፈውን ፍርድ ለመፈጸም ነው።

ለቅዱሳኑም ሁሉ ይህች ክብር ናት።

ሃሌ ሉያ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 149:1-9

149

1ハレルヤ。

主をほめたたえ、新しい歌を歌いましょう。

神の民よ。賛美の歌声を上げなさい。

2イスラエルよ、あなたを造られた主を喜びなさい。

エルサレムの人々よ、王であるお方の前で喜びなさい。

3タンバリンと竪琴の伴奏で、

踊りながら神の御名をほめたたえなさい。

4-5主はご自分の民を喜んで受け入れ、

謙虚な者を救ってくださるのです。

この光栄を思い浮かべて、

神の民が感謝しますように。

寝床でも、喜びのあまり歌いだしますように。

6-7神の民よ、主をあがめなさい。

神に代わって両刃の剣を取り、国々を罰しなさい。

8王や指導者を鉄の鎖で縛り上げ、

9宣告されたとおりに処罰しなさい。

神の民の栄光は神ご自身です。

ハレルヤ。主をほめたたえましょう。