መዝሙር 145 – NASV & NRT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 145:1-21

መዝሙር 145145 ይህ መዝሙር ተከታታይ በሆኑ የዕብራይስጥ ፊደላት የሚጀምር ሲሆን፣ (ከ13 ጭምር) መነሻዎቹ ወይም መነሻዎቹና መድረሻዎቹ ሆህያት ቍልቍል ሲነበቡ ትርጕም ያላቸውን ቃላት የሚፈጥሩ ናቸው።

ምስጋና ለንጉሡ ለእግዚአብሔር

የዳዊት የምስጋና መዝሙር።

1አምላኬና ንጉሤ ሆይ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤

ስምህን ከዘላለም እስከ ዘላለም እባርካለሁ።

2በየቀኑ እባርክሃለሁ፤

ስምህንም ከዘላለም እስከ ዘላለም አመሰግናለሁ።

3እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤ እጅግ ሊመሰገንም ይገባዋል፤

ታላቅነቱም አይመረመርም።

4ሥራህን አንዱ ትውልድ ለሌላው ትውልድ ያስተጋባል፤

ብርቱ ሥራህን ያውጃል።

5ስለ ግርማህ ውበትና ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ድንቅ ሥራህም145፥5 የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) ስለ ግርማህ ታላቅነትና ክብር፣ ዕፁብ ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ ይላሉ። ያወራሉ።

6ስለ ድንቅ ሥራህ ብርታት ይነጋገራሉ፤

እኔም ስለ ታላቅነትህ ዐውጃለሁ።

7የበጎነትህን ብዛት በደስታ ያወሳሉ፤

ስለ ጽድቅህም በእልልታ ይዘምራሉ።

8እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ርኅሩኅም ነው፤

ለቍጣ የዘገየ፣ ምሕረቱ የበዛ።

9እግዚአብሔር ለሁሉ ቸር ነው፤

ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው።

10እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍጥረትህ ሁሉ ያመሰግንሃል፤

ቅዱሳንህም ይባርኩሃል።

11ስለ መንግሥትህ ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ኀይልህም ይነጋገራሉ፤

12በዚህም ብርቱ ሥራህን፣

የመንግሥትህንም ግርማ ክብር ያስታውቃሉ።

13መንግሥትህ የዘላለም መንግሥት ናት፤

ግዛትህም ለትውልድ ሁሉ ጸንቶ ይኖራል።

እግዚአብሔር ቃሉን ሁሉ ይጠብቃል፤

በሥራውም145፥13 አንድ የማስሬቲክ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) እንዲሁም አብዛኛው የማስሬቲክ ቅጆች የ13 ሁለት ስንኞች የሏቸውም። ሁሉ ቸር ነው።

14እግዚአብሔር የሚንገዳገዱትን ሁሉ ይደግፋል፤

የወደቁትንም ሁሉ ያነሣል።

15የሁሉ ዐይን አንተን በተስፋ ይጠብቃል፤

አንተም ምግባቸውን በወቅቱ ትሰጣቸዋለህ።

16አንተ እጅህን ትዘረጋለህ፤

የሕያዋን ፍጥረታትንም ሁሉ ፍላጎት ታረካለህ።

17እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ፣

በሥራውም ሁሉ ቸር ነው።

18እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፣

በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።

19ለሚፈሩት ፍላጎታቸውን ይፈጽማል፤

ጩኸታቸውን ይሰማል፤ ያድናቸዋልም።

20እግዚአብሔር የሚወድዱትን ሁሉ ይጠብቃል፤

ክፉዎችን ሁሉ ግን ያጠፋል።

21አፌ የእግዚአብሔርን ምስጋና ይናገራል፤

ፍጡር ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ ቅዱስ ስሙን ይባርክ።

New Russian Translation

Псалтирь 145:1-10

Псалом 145

1Аллилуйя!

Восхваляй, душа моя, Господа!

2Всю свою жизнь буду восхвалять Господа;

буду петь хвалу моему Богу, пока я жив.

3Не надейтесь на правителей,

на человека, в котором нет спасения.

4Когда дух покидает его, и он возвращается в землю,

в тот самый день исчезают и все его помышления.

5Блажен тот, кому помощник Бог Иакова,

кто надеется на Господа, своего Бога,

6сотворившего небо и землю,

море и все, что его наполняет, –

Он вечно хранит Свою верность.

7Он защищает дело угнетенных,

дает пищу голодным.

Господь освобождает заключенных.

8Господь открывает глаза слепым,

Господь поднимает всех низверженных,

Господь любит праведных.

9Господь хранит чужеземцев,

поддерживает сирот и вдов,

а путь нечестивых искривляет.

10Господь царствует вовек,

Твой Бог, Сион, – во все поколения.

Аллилуйя!