መዝሙር 145 – NASV & CARST

New Amharic Standard Version

መዝሙር 145:1-21

መዝሙር 145145 ይህ መዝሙር ተከታታይ በሆኑ የዕብራይስጥ ፊደላት የሚጀምር ሲሆን፣ (ከ13 ጭምር) መነሻዎቹ ወይም መነሻዎቹና መድረሻዎቹ ሆህያት ቍልቍል ሲነበቡ ትርጕም ያላቸውን ቃላት የሚፈጥሩ ናቸው።

ምስጋና ለንጉሡ ለእግዚአብሔር

የዳዊት የምስጋና መዝሙር።

1አምላኬና ንጉሤ ሆይ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤

ስምህን ከዘላለም እስከ ዘላለም እባርካለሁ።

2በየቀኑ እባርክሃለሁ፤

ስምህንም ከዘላለም እስከ ዘላለም አመሰግናለሁ።

3እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤ እጅግ ሊመሰገንም ይገባዋል፤

ታላቅነቱም አይመረመርም።

4ሥራህን አንዱ ትውልድ ለሌላው ትውልድ ያስተጋባል፤

ብርቱ ሥራህን ያውጃል።

5ስለ ግርማህ ውበትና ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ድንቅ ሥራህም145፥5 የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) ስለ ግርማህ ታላቅነትና ክብር፣ ዕፁብ ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ ይላሉ። ያወራሉ።

6ስለ ድንቅ ሥራህ ብርታት ይነጋገራሉ፤

እኔም ስለ ታላቅነትህ ዐውጃለሁ።

7የበጎነትህን ብዛት በደስታ ያወሳሉ፤

ስለ ጽድቅህም በእልልታ ይዘምራሉ።

8እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ርኅሩኅም ነው፤

ለቍጣ የዘገየ፣ ምሕረቱ የበዛ።

9እግዚአብሔር ለሁሉ ቸር ነው፤

ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው።

10እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍጥረትህ ሁሉ ያመሰግንሃል፤

ቅዱሳንህም ይባርኩሃል።

11ስለ መንግሥትህ ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ኀይልህም ይነጋገራሉ፤

12በዚህም ብርቱ ሥራህን፣

የመንግሥትህንም ግርማ ክብር ያስታውቃሉ።

13መንግሥትህ የዘላለም መንግሥት ናት፤

ግዛትህም ለትውልድ ሁሉ ጸንቶ ይኖራል።

እግዚአብሔር ቃሉን ሁሉ ይጠብቃል፤

በሥራውም145፥13 አንድ የማስሬቲክ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) እንዲሁም አብዛኛው የማስሬቲክ ቅጆች የ13 ሁለት ስንኞች የሏቸውም። ሁሉ ቸር ነው።

14እግዚአብሔር የሚንገዳገዱትን ሁሉ ይደግፋል፤

የወደቁትንም ሁሉ ያነሣል።

15የሁሉ ዐይን አንተን በተስፋ ይጠብቃል፤

አንተም ምግባቸውን በወቅቱ ትሰጣቸዋለህ።

16አንተ እጅህን ትዘረጋለህ፤

የሕያዋን ፍጥረታትንም ሁሉ ፍላጎት ታረካለህ።

17እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ፣

በሥራውም ሁሉ ቸር ነው።

18እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፣

በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።

19ለሚፈሩት ፍላጎታቸውን ይፈጽማል፤

ጩኸታቸውን ይሰማል፤ ያድናቸዋልም።

20እግዚአብሔር የሚወድዱትን ሁሉ ይጠብቃል፤

ክፉዎችን ሁሉ ግን ያጠፋል።

21አፌ የእግዚአብሔርን ምስጋና ይናገራል፤

ፍጡር ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ ቅዱስ ስሙን ይባርክ።

Священное Писание (Восточный перевод), версия для Таджикистана

Забур 145:1-10

Песнь 145

1Славьте Вечного!

Восхваляй, душа моя, Вечного!

2Всю свою жизнь буду восхвалять Вечного;

буду петь хвалу моему Богу, пока я жив.

3Не надейтесь на правителей,

они всего лишь люди и не могут вас спасти.

4Когда дух покидает их, и они возвращаются в землю,

в тот самый день исчезают и все их помышления.

5Благословен тот, кому помощник Бог Якуба,

кто надеется на Вечного, своего Бога,

6сотворившего небо и землю,

море и всё, что его наполняет, –

на Вечного, Который хранит Свою верность вовеки.

7Он защищает дело угнетённых,

даёт пищу голодным.

Вечный освобождает заключённых,

8Вечный открывает глаза слепым,

Вечный поднимает всех низверженных,

Вечный любит праведных.

9Вечный хранит чужеземцев,

поддерживает сирот и вдов,

а путь нечестивых искривляет.

10Вечный будет царствовать вовеки,

Твой Бог, Сион, – во все поколения.

Славьте Вечного!