መዝሙር 144 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 144:1-15

መዝሙር 144

የጦርነት መዝሙር

የዳዊት መዝሙር።

1እጆቼን ለጦርነት፣ ጣቶቼን ለውጊያ የሚያሠለጥን፣

እግዚአብሔር ዐለቴ ይባረክ።

2እርሱ አፍቃሪ አምላኬና ጽኑ ዐምባዬ ነው፤

ምሽጌና ታዳጊዬ፣

የምከለልበትም ጋሻዬ ነው፤

ሕዝቤን የሚያስገዛልኝም144፥2 አንዳንዶች ሕዝቦችን የሚያሰገዛልኝ ይላሉ። እርሱ ነው።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህን ያህል በልብህ ስፍራ ትሰጠው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

ታስበውስ ዘንድ የሰው ልጅ እስከዚህ ምንድን ነው?

4ሰው እንደ እስትንፋስ ነው፤

ዘመኑም ፈጥኖ እንደሚያልፍ ጥላ ነው።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰማያትህን ሰንጥቀህ ውረድ፤

ይጤሱም ዘንድ ተራሮችን ዳስስ።

6የመብረቅ ብልጭታ ልከህ በትናቸው፤

ፍላጻህን ሰድደህ ግራ አጋባቸው።

7እጅህን ከላይ ዘርጋ፤

ከኀይለኛ ውሃ፣

ከባዕዳንም እጅ

ታደገኝ፤ አድነኝም።

8አንደበታቸው ሐሰትን ይናገራል፤

ቀኝ እጃቸውም የቅጥፈት ቀኝ እጅ ናት።

9አምላክ ሆይ፤ አዲስ ቅኔ እቀኝልሃለሁ፤

ዐሥር አውታር ባለው በገና እዘምርልሃለሁ።

10ነገሥታትን ድል የሚያጐናጽፍ፣

ባሪያውን ዳዊትን ከሚጐዳ ሰይፍ የሚያድነው እርሱ ነው።

11አንደበታቸው ሐሰትን ከሚናገር፣

ቀኝ እጃቸው የቅጥፈት ቀኝ እጅ ከሆነችው፣

ከባዕዳን እጅ

ታደገኝ፤ አድነኝም።

12ወንዶች ልጆቻችን በወጣትነታቸው፣

የተሟላ ዕድገት እንዳገኘ ተክል፣

ሴቶች ልጆቻችንም ቤተ መንግሥት ለማስጌጥ

እንደ ተቀረጹ የማእዘን ዐምዶች ይሁኑ።

13ጐተራዎቻችን በተለያየ የእህል ዐይነት፣

የተሞሉ ይሁኑ፤

በጎቻችን እስከ ሺሕ ይውለዱ፤

በመስኮቻችንም እስከ ዐሥር ሺሕ ይባዙ።

14ከብቶቻችን ይክበዱ፤144፥14 ወይም መሪዎቻችን ይጠነክራሉ

አይጨንግፉ፤ አይጥፉም።

እኛም በምርኮ አንወሰድ፤

በአደባባዮቻችንም ዋይታ አይሰማ።

15ይህ ባርኮት ገንዘቡ የሆነ ሕዝብ ምስጉን ነው፤

እግዚአብሔር አምላኩ የሆነ ሕዝብ ምስጉን ነው።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 144:1-15

144

1揺るぎない岩である主をほめたたえます。

戦いが起こると、主は、

弓をひく私の腕を強めてくださいます。

2いつも恵み深く、愛を注いでくださる主は、

私の要塞であり、びくともしないやぐらです。

私を救ってくださる神は、

盾となって立ちはだかってくださいます。

こうして、神は

民を私に服従させてくださるのです。

3主よ。あなたが気に留めてくださるのは、

人間が何者だからなのでしょう。

どうしてあなたは、

こんな人間にかかわってくださるのでしょう。

4人の一生は、ただのひと呼吸のよう、

また影のようで、はかなく消えるではありませんか。

5主よ、どうか、天を押し曲げて降りて来てください。

あなたの手が山に触れると、煙が吹き出します。

6主よ、いなずまの矢を敵に放ち、

彼らを散らすように蹴散らしてください。

7天から御手を差し伸べ、私を引き上げてください。

深い水の中から、強い敵の腕から、

助け出してください。

8彼らの口はうそで満ち、

間違っていることをほんとうだと言い張ります。

9ああ神よ。私は十弦の琴をかなで、

あなたに新しい歌をささげます。

10あなたは王に勝利をもたらされるお方です。

あなたのしもべダビデを、

悪の剣から救い出されるお方です。

11どうか、悪賢い敵から、私を救い出してください。

12-15神を信じる国の祝福された様子を語りましょう。

男の子は、すくすくと成長する木のように、

元気いっぱいに育ちます。

女の子は、宮殿にふさわしく飾られた柱のように、

しとやかで優雅です。

倉には穀物がこれ以上入らないほど

豊かにあります。

羊の群れは、何千頭、何万頭と増え、

牛は次々と子どもを産みます。

敵は一人も攻めて来ず、平和が満ちあふれています。

町には一つの犯罪も起こりません。

このように、主を神とする民は幸いです。