መዝሙር 141 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 141:1-10

መዝሙር 141

የክፉዎችን ድሎት ላለመመኘት የቀረበ ጸሎት

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤ ፈጥነህ ድረስልኝ፤

ወደ አንተ ስጣራም ድምፄን ስማ።

2ጸሎቴ በፊትህ እንደ ዕጣን ትቈጠርልኝ፤

እጄን ማንሣቴም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ለአፌ ጠባቂ አድርግ፤

የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ።

4ከዐመፀኞች ጋር፣

በክፉ ሥራ እንዳልተባበር፣

ልቤን ወደ ክፉ አታዘንብል፤

ከድግሳቸውም አልቋደስ።

5ጻድቅ141፥5 ወይም ጻድቁ ሰው ይቅጣኝ፤ ይህ በጎነት ነው፤

ይገሥጸኝም፤ በራሴ ላይ እንደሚፈስስ ዘይት ነው፤

ራሴም ይህን እንቢ አይልም።

ጸሎቴ ግን በክፉዎች ተግባር ላይ ነው፤

6ሹማምታቸው ከገደል አፋፍ ቍልቍል ይወረወራሉ፤

ቃሌ የምታረካ ናትና ይሰሟታል።

7ደግሞም፣ “ሰው ምድርን እንደሚያርስና ዐፈሩን እንደሚፈረካክስ፣

እንዲሁ ዐጥንታችን በሲኦል141፥7 አንዳንድ ትርጕሞች መቃብር ይላሉ። አፋፍ ላይ ተበታተነ” ይላሉ።

8ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐይኖቼ ግን ወደ አንተ ይመለከታሉ፤

መጠጊያዬም አንተ ነህ፤ እንግዲህ ነፍሴን አትተዋት።

9ከዘረጉብኝ ወጥመድ፣

ከክፉ አድራጊዎችም አሽክላ ጠብቀኝ።

10እኔ ብቻ በደኅና ሳመልጥ፣

ክፉዎቹ በገዛ ወጥመዳቸው ይውደቁ።

Ketab El Hayat

مزمور 141:1-10

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالْحَادِي وَالأَرْبَعُونَ

مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1يَا رَبُّ إِلَيْكَ دَعَوْتُ، فَأَسْرِعْ لإِغَاثَتِي. أَصْغِ إِلَى صَوْتِي عِنْدَمَا أَصْرُخُ إِلَيْكَ. 2لِتَكُنْ صَلاتِي أَمَامَكَ كَالْبَخُورِ، وَرَفْعُ يَدَيَّ مِثْلَ تَقْدِمَةِ الْمَسَاءِ. 3أَقِمْ يَا رَبُّ حَارِساً لِفَمِي، وَاحْفَظْ بَابَ شَفَتَيَّ. 4لَا تَدَعْ قَلْبِي يَتَعَلَّقُ بِشَيْءٍ رَدِيءٍ، فَيُمَارِسَ أَعْمَالَ الشَّرِّ مَعَ فَاعِلِي الإِثْمِ. وَلَا تَدَعْنِي آكُلُ مِنْ أَطَايِبِهِمْ.

5لِيَضْرِبْنِي الصِّدِّيقُ فَذَلِكَ رَحْمَةٌ، وَلْيُوَبِّخْنِي فَذَلِكَ زَيْتٌ عَاطِرٌ لِرَأْسِي. أَمَّا الأَشْرَارُ فَإِنِّي أُصَلِّي دَائِماً (كَي تَحْفَظَنِي مِنْ أَفْعَالِهِمِ الأَثِيمَةِ). 6عِنْدَمَا يُلْقَى بِقُضَاتِهِمِ الظَّالِمِينَ مِنْ عَلَى الصَّخْرَةِ، آنَئِذٍ يَسْمَعُونَ لِكَلِمَاتِي إِذْ يُوْقِنُونَ أَنَّهَا حَقٌّ. 7تَتَنَاثَرُ عِظَامُهُمْ عِنْدَ فَمِ الْقَبْرِ كَشَظَايَا الْحَطَبِ الْمُشَقَّقَةِ الْمُبَعْثَرَةِ عَلَى الأَرْضِ. 8لَكِنَّ نَحْوَكَ أَيُّهَا الرَّبُّ السَّيِّدُ رَفَعْتُ عَيْنَيَّ، وَبِكَ لُذْتُ، فَلَا تَتْرُكْ نَفْسِي عُرْضَةً لِلْمَوْتِ. 9احْفَظْنِي مِنَ الْفَخِّ الَّذِي نَصَبُوهُ لِي، وَمِنْ أَشْرَاكِ فَاعِلِي الإِثْمِ. 10لِيَسْقُطِ الأَشْرَارُ فِي أَشْرَاكِهِمْ حَتَّى أَنْجُوَ تَمَامَ النَّجَاةِ.