መዝሙር 14 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 14:1-7

መዝሙር 14

አምላክ የለሽ ሰዎች

14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሞኝ14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።

2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤

በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤

አንድ እንኳ፣

መልካም የሚያደርግ የለም።

4የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣

ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?

5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤

እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።

6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤

እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።

7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 14:1-7

14

1心の中で「神などいない」と言う者は愚かです。

彼の心は腐っており、

正しい人であるはずがありません。

2主は天からすべての人々を見下ろし、

神を喜ばせたいと願う

賢い者をお探しになります。

3しかし、だれもいないのです。

すべての人が道を踏みはずし、

罪のために腐りきっています。

正しい人はいません。ただの一人もいません。

4彼らはわたしの民をパンのように食べ、

主に祈ろうなどとは考えもしない。

彼らに良心のかけらもないのか。

5彼らは恐怖に取りつかれることになります。

神はご自分を愛する者とともにおられるからです。

6貧しい者や謙遜な者が悪者に虐待されるとき、

神は避け所となってくださいます。

7ああ、今すぐ救いの時がきますように。

ご自分の民を救うため、主がすぐに、

シオン(エルサレム)から

駆けつけてくださいますように。

ああ、イスラエルが救い出されるときは、

どれほどの喜びがもたらされることでしょう。