መዝሙር 14 – NASV & CST

New Amharic Standard Version

መዝሙር 14:1-7

መዝሙር 14

አምላክ የለሽ ሰዎች

14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሞኝ14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።

2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤

በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤

አንድ እንኳ፣

መልካም የሚያደርግ የለም።

4የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣

ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?

5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤

እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።

6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤

እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።

7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።

Nueva Versión Internacional (Castilian)

Salmo 14:1-7

Salmo 14

14:1-7Sal 53:1-6

Al director musical. Salmo de David.

1Dice el necio en su corazón:

«No hay Dios».

Están corrompidos, sus obras son detestables;

¡no hay uno solo que haga lo bueno!

2Desde el cielo, el Señor contempla a los mortales,

para ver si hay alguien

que sea sensato y busque a Dios.

3Pero todos se han descarriado,

a una se han corrompido.

No hay nadie que haga lo bueno;

¡no hay uno solo!

4¿Acaso no tienen entendimiento todos los que hacen lo malo,

los que devoran a mi pueblo como si fuera pan?

¡Jamás invocan al Señor!

5Allí los tenéis, sobrecogidos de miedo,

pero Dios está con los que son justos.

6Vosotros frustráis los planes de los pobres,

pero el Señor los protege.

7¡Quiera Dios que de Sión

venga la salvación de Israel!

Cuando el Señor restaure a su pueblo,14:7 restaure a su pueblo. Alt. haga que su pueblo vuelva del cautiverio.

¡Jacob se regocijará, Israel se alegrará!