መዝሙር 137 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 137:1-9

መዝሙር 137

የግዞተኞች ቅኔ

1በባቢሎን ወንዞች አጠገብ፣ በዚያ ተቀምጠን ሳለን፣

ጽዮን ትዝ ባለችን ጊዜ አለቀስን።

2እዚያም በአኻያ ዛፎች ላይ፣

በገናዎቻችንን ሰቀልን።

3የማረኩን በዚያ እንድንዘምርላቸው ጠየቁን፤

የሚያሠቃዩን የደስታ ዜማ ፈለጉብን፤

ደግሞም፣ “ከጽዮን መዝሙሮች አንዱን ዘምሩልን” አሉን።

4የእግዚአብሔርን ዝማሬ፣

እንዴት በባዕድ ምድር እንዘምር!

5ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ብረሳሽ፣

ቀኝ እጄ ትክዳኝ።

6ሳላስታውስሽ ብቀር፣

ኢየሩሳሌምን የደስታዬ ቍንጮ ባላደርግ፣

ምላሴ ከትናጋዬ ጋር ትጣበቅ።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ኢየሩሳሌም በወደቀችበት ቀን፣

ኤዶማውያን እንዴት እንደ ዛቱ ዐስብ፤

ደግሞም፣ “አፍርሷት፤

ፈጽማችሁ አፈራርሷት!” አሉ።

8አንቺ አጥፊ የሆንሽ የባቢሎን ልጅ ሆይ፤

በእኛ ላይ ስለ ፈጸምሽው ድርጊት፣

የእጅሽን የሚሰጥሽ የተመሰገነ ነው፤

9ሕፃናትሽንም ይዞ፣

በዐለት ላይ የሚፈጠፍጥ የተመሰገነ ነው።

Ketab El Hayat

مزمور 137:1-9

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالسَّابِعُ وَالثَّلاثُونَ

1عَلَى ضِفَافِ أَنْهَارِ بَابِلَ جَلَسْنَا، وَبَكَيْنَا عِنْدَمَا تَذَكَّرْنَا أُورُشَلِيمَ. 2هُنَاكَ عَلَّقْنَا أَعْوَادَنَا عَلَى أَشْجَارِ الصَّفْصَافِ. 3هُنَاكَ طَلَبَ مِنَّا الَّذِينَ سَبَوْنَا أَنْ نَشْدُوَ بِتَرْنِيمَةٍ، وَالَّذِينَ عَذَّبُونَا أَنْ نُطْرِبَهُمْ قَائِلِينَ: «أَنْشِدُوا لَنَا مِنْ تَرَانِيمِ صِهْيَوْنَ».

4كَيْفَ نَشْدُو بِتَرْنِيمَةِ الرَّبِّ فِي أَرْضٍ غَرِيبَةٍ؟ 5إِنْ نَسِيتُكِ يَا أُورُشَلِيمُ، فَلْتَنْسَ يَمِينِي مَهَارَتَهَا. 6لِيَلْتَصِقْ لِسَانِي بِحَنَكِي إِنْ لَمْ أَذْكُرْكِ وَلَمْ أُفَضِّلْكِ عَلَى ذِرْوَةِ أَفْرَاحِي.

7اذْكُرْ يَا رَبُّ لِبَنِي أَدُومَ مَا فَعَلُوهُ يَوْمَ خَرَابِ أُورُشَلِيمَ، إِذْ قَالُوا: «اهْدِمُوا اهْدِمُوا حَتَّى يَتَعَرَّى أَسَاسُهَا». 8يَا بِنْتَ بَابِلَ الْمُحَتَّمِ خَرَابُهَا، طُوبَى لِمَنْ يُجَازِيكِ بِمَا جَزَيْتِنَا بِهِ. 9طُوبَى لِمَنْ يُمْسِكُ صِغَارَكِ وَيَضْرِبُ بِهِمِ الصَّخْرَةَ.