መዝሙር 135 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 135:1-21

መዝሙር 135

የምስጋና መዝሙር

135፥15-20 ተጓ ምብ – መዝ 115፥4-11

1ሃሌ ሉያ።135፥1 3 እና 21 ጭምር በአንዳንድ ትርጕሞች እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

የእግዚአብሔርን ስም ወድሱ፤

እናንት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

2በእግዚአብሔር ቤት፣

በአምላካችን ቤት አደባባይ የምትቆሙ አመስግኑት።

3እግዚአብሔር ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

መልካም ነውና፣ ለስሙ ዘምሩ፤

4እግዚአብሔር ያዕቆብን ለራሱ፣

እስራኤልንም ውድ ንብረቱ አድርጎ መርጧልና።

5እግዚአብሔር ታላቅ እንደ ሆነ፣

ጌታችንም ከአማልክት ሁሉ እንደሚበልጥ ዐውቃለሁና።

6በሰማይና በምድር፣

በባሕርና በጥልቅ ሁሉ ውስጥ፣

እግዚአብሔር ደስ ያሰኘውን ሁሉ ያደርጋል።

7እርሱ ደመናትን ከምድር ዳርቻ ያስነሣል፤

መብረቅ ከዝናብ ጋር እንዲወርድ ያደርጋል፤

ነፋሳትንም ከማከማቻው ያወጣል።

8በኵር ሆኖ በግብፅ የተወለደውን፣

ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ ቀሠፈ።

9ግብፅ ሆይ፤ በፈርዖንና በአገልጋዮቹ ሁሉ ላይ፣

በመካከልሽ ታምራትንና ድንቅን ሰደደ።

10ብዙ ሕዝቦችን መታ፤

ኀያላን ነገሥታትንም ገደለ።

11የአሞራውያንን ንጉሥ ሴዎንን፣

የባሳንን ንጉሥ ዐግን፣

የከነዓንን ነገሥታት ሁሉ ገደለ፤

12ምድራቸውንም ርስት አድርጎ፣

ለሕዝቡ ርስት እንዲሆን ለእስራኤል ሰጠ።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህ ዘላለማዊ ነው፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መታሰቢያህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

14እግዚአብሔር ለሕዝቡ ይፈርዳልና፣

ለአገልጋዮቹም ይራራላቸዋል።

15የአሕዛብ ጣዖታት ከብርና ከወርቅ የተሠሩ፣

የሰው እጅ ያበጃቸው ናቸው።

16አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፤

17ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

በአፋቸውም እስትንፋስ የለም።

18እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

19የእስራኤል ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

የአሮን ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

20የሌዊ ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ።

21በኢየሩሳሌም የሚኖር እግዚአብሔር፣ ከጽዮን ይባረክ።

ሃሌ ሉያ።

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 135:1-21

Psalm 135

En lovsång som prisar Herrens under

1Halleluja!

Prisa Herrens namn,

prisa honom, ni Herrens tjänare,

2ni som står i Herrens hus,

på förgårdarna till vår Guds hus.

3Prisa Herren, för han är god!

Lovsjung hans namn,

för det är underbart.

4Herren har utvalt Jakob åt sig

och Israel till sin egendom.

5Jag vet att Herren är stor,

vår Herre är större än alla gudar.

6Herren gör allt vad han vill

både i himlen och på jorden, i haven och i djupen.

7Han låter molnen stiga upp vid horisonten,

han sänder blixt och regn

och han sänder ut vindarna från sina förråd.

8I Egypten dödade han de förstfödda

bland både människor och djur.

9Han sände tecken och under till Egypten,

till farao och dennes tjänstefolk.

10Han besegrade många folk

och dödade mäktiga kungar,

11Sichon, amoréernas kung,

Og, Bashans kung

och alla Kanaans kungar.

12Han gav deras länder

som en arvslott till sitt folk Israel.

13Herre, ditt namn består i evighet.

I alla tider kommer man att minnas dig, Herre.

14Herren skaffar rätt åt sitt folk

och förbarmar sig över sina tjänare.

15Folkens gudar är silver och guld,

verk av människohänder.

16De har munnar som inte kan tala

och ögon som inte kan se.

17De har öron som inte kan höra,

och i deras munnar finns ingen andedräkt.

18De som har gjort dem ska bli som de,

liksom alla som sätter sin lit till dem.

19Israels släkt, prisa Herren!

Arons släkt, prisa Herren!

20Levis släkt, prisa Herren!

Prisa Herren, ni som fruktar honom!

21Prisad vare Herren från Sion,

han som bor i Jerusalem.

Halleluja!