መዝሙር 135 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 135:1-21

መዝሙር 135

የምስጋና መዝሙር

135፥15-20 ተጓ ምብ – መዝ 115፥4-11

1ሃሌ ሉያ።135፥1 3 እና 21 ጭምር በአንዳንድ ትርጕሞች እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

የእግዚአብሔርን ስም ወድሱ፤

እናንት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

2በእግዚአብሔር ቤት፣

በአምላካችን ቤት አደባባይ የምትቆሙ አመስግኑት።

3እግዚአብሔር ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

መልካም ነውና፣ ለስሙ ዘምሩ፤

4እግዚአብሔር ያዕቆብን ለራሱ፣

እስራኤልንም ውድ ንብረቱ አድርጎ መርጧልና።

5እግዚአብሔር ታላቅ እንደ ሆነ፣

ጌታችንም ከአማልክት ሁሉ እንደሚበልጥ ዐውቃለሁና።

6በሰማይና በምድር፣

በባሕርና በጥልቅ ሁሉ ውስጥ፣

እግዚአብሔር ደስ ያሰኘውን ሁሉ ያደርጋል።

7እርሱ ደመናትን ከምድር ዳርቻ ያስነሣል፤

መብረቅ ከዝናብ ጋር እንዲወርድ ያደርጋል፤

ነፋሳትንም ከማከማቻው ያወጣል።

8በኵር ሆኖ በግብፅ የተወለደውን፣

ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ ቀሠፈ።

9ግብፅ ሆይ፤ በፈርዖንና በአገልጋዮቹ ሁሉ ላይ፣

በመካከልሽ ታምራትንና ድንቅን ሰደደ።

10ብዙ ሕዝቦችን መታ፤

ኀያላን ነገሥታትንም ገደለ።

11የአሞራውያንን ንጉሥ ሴዎንን፣

የባሳንን ንጉሥ ዐግን፣

የከነዓንን ነገሥታት ሁሉ ገደለ፤

12ምድራቸውንም ርስት አድርጎ፣

ለሕዝቡ ርስት እንዲሆን ለእስራኤል ሰጠ።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህ ዘላለማዊ ነው፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መታሰቢያህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

14እግዚአብሔር ለሕዝቡ ይፈርዳልና፣

ለአገልጋዮቹም ይራራላቸዋል።

15የአሕዛብ ጣዖታት ከብርና ከወርቅ የተሠሩ፣

የሰው እጅ ያበጃቸው ናቸው።

16አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፤

17ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

በአፋቸውም እስትንፋስ የለም።

18እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

19የእስራኤል ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

የአሮን ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

20የሌዊ ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ።

21በኢየሩሳሌም የሚኖር እግዚአብሔር፣ ከጽዮን ይባረክ።

ሃሌ ሉያ።

Korean Living Bible

시편 135:1-21

찬양의 대상인 여호와

1여호와를 찬양하라!

여호와의 종들아,

그의 이름을 찬양하라.

2여호와의 집에서,

우리 하나님의 성전 뜰에서

섬기는 자들아,

그를 찬양하라.

3여호와는 선하시니 그를 찬양하고

그의 아름다운 이름을 찬송하라.

4여호와께서 자기를 위해

야곱을 택하시고

이스라엘 백성을

자기 소유로 삼으셨다.

5여호와는 위대하시고

모든 신보다 뛰어난 분이시다.

6여호와께서는

하늘과 땅과 바다에서

원하시는 것은 무엇이든지

다 행하신다.

7그는 땅 끝에서 구름을 일으키시며

비를 위해 번개를 보내시고

그의 창고에서 바람을 내신다.

8그가 이집트의 첫태생을

사람으로부터 짐승까지

모조리 죽이시고

9또 이집트에서

기적과 놀라운 일을 행하셔서

바로와 그 신하들을 벌하셨다.

10그가 많은 나라를 치시고

강한 왕들을 죽이셨으니

11아모리 사람의 왕 시혼과

바산 왕 옥과

가나안의 모든 왕들이었다.

12그가 저들의 땅을

자기 백성 이스라엘에게

영원한 선물로 주셨다.

13여호와여, 주의 이름은

영원히 남을 것이며

모든 세대가 주를 기억할 것입니다.

14여호와께서 자기 백성을

변호할 것이며

자기 종들을 불쌍히 여기시리라.

15이방 민족의 신들은 은과 금이며

사람의 손으로 만든

우상에 불과하다.

16그들은 입이 있어도 말하지 못하며

눈이 있어도 보지 못하고

17귀가 있어도 듣지 못한다.

또 그 입에는 입김도 없으니

18그것을 만든 자와

그것을 신뢰하는 자들이

다 그와 같으리라.

19이스라엘 백성아,

여호와를 찬양하라!

135:19 또는 ‘아론의 족속아’여호와의 제사장들아,

여호와를 찬양하라!

20레위 사람들아,

여호와를 찬양하라!

여호와를 두려워하는 자들아,

그를 찬양하라!

21시온 사람들아, 예루살렘에 계시는

여호와를 찬양하라!

여호와를 찬양하라!