መዝሙር 135 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 135:1-21

መዝሙር 135

የምስጋና መዝሙር

135፥15-20 ተጓ ምብ – መዝ 115፥4-11

1ሃሌ ሉያ።135፥1 3 እና 21 ጭምር በአንዳንድ ትርጕሞች እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

የእግዚአብሔርን ስም ወድሱ፤

እናንት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

2በእግዚአብሔር ቤት፣

በአምላካችን ቤት አደባባይ የምትቆሙ አመስግኑት።

3እግዚአብሔር ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

መልካም ነውና፣ ለስሙ ዘምሩ፤

4እግዚአብሔር ያዕቆብን ለራሱ፣

እስራኤልንም ውድ ንብረቱ አድርጎ መርጧልና።

5እግዚአብሔር ታላቅ እንደ ሆነ፣

ጌታችንም ከአማልክት ሁሉ እንደሚበልጥ ዐውቃለሁና።

6በሰማይና በምድር፣

በባሕርና በጥልቅ ሁሉ ውስጥ፣

እግዚአብሔር ደስ ያሰኘውን ሁሉ ያደርጋል።

7እርሱ ደመናትን ከምድር ዳርቻ ያስነሣል፤

መብረቅ ከዝናብ ጋር እንዲወርድ ያደርጋል፤

ነፋሳትንም ከማከማቻው ያወጣል።

8በኵር ሆኖ በግብፅ የተወለደውን፣

ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ ቀሠፈ።

9ግብፅ ሆይ፤ በፈርዖንና በአገልጋዮቹ ሁሉ ላይ፣

በመካከልሽ ታምራትንና ድንቅን ሰደደ።

10ብዙ ሕዝቦችን መታ፤

ኀያላን ነገሥታትንም ገደለ።

11የአሞራውያንን ንጉሥ ሴዎንን፣

የባሳንን ንጉሥ ዐግን፣

የከነዓንን ነገሥታት ሁሉ ገደለ፤

12ምድራቸውንም ርስት አድርጎ፣

ለሕዝቡ ርስት እንዲሆን ለእስራኤል ሰጠ።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህ ዘላለማዊ ነው፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መታሰቢያህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

14እግዚአብሔር ለሕዝቡ ይፈርዳልና፣

ለአገልጋዮቹም ይራራላቸዋል።

15የአሕዛብ ጣዖታት ከብርና ከወርቅ የተሠሩ፣

የሰው እጅ ያበጃቸው ናቸው።

16አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፤

17ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

በአፋቸውም እስትንፋስ የለም።

18እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

19የእስራኤል ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

የአሮን ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

20የሌዊ ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ።

21በኢየሩሳሌም የሚኖር እግዚአብሔር፣ ከጽዮን ይባረክ።

ሃሌ ሉያ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 135:1-21

第 135 篇

讚美之歌

(平行經文:詩篇115·4-11

1-2你們要讚美耶和華!

讚美祂的名!

耶和華的僕人啊,

在耶和華的殿中,

在我們上帝的院宇中事奉的人啊,

你們要讚美祂!

3你們要讚美耶和華,

因為祂是美善的;

你們要歌頌祂的名,

因為祂的名美好無比。

4祂揀選雅各做祂的子民,

揀選以色列作祂的產業。

5我知道耶和華偉大,

我們的主超越一切神明。

6耶和華在天上、地下、海洋、

深淵按自己的旨意行事。

7祂使雲霧從地極上升,

發出電光,帶來雨水,

從祂的倉庫帶出風來。

8祂擊殺了埃及人的長子和頭胎的牲畜。

9祂在埃及行神蹟奇事,

懲罰法老和他的一切臣僕。

10祂毀滅列國,

殺戮強大的君王:

11亞摩利西宏巴珊迦南所有的君王。

12祂把這些國家的土地賜給祂的以色列子民,

作為他們的產業。

13耶和華啊,

你的名永遠長存,

你的威名傳到萬代。

14因為耶和華必為祂的子民伸冤,

憐憫祂的僕人。

15外族人的神像是人用金銀造的。

16它們有口不能說,有眼不能看,

17有耳不能聽,口中毫無氣息。

18那些製造它們、信靠它們的人也會和它們一樣。

19以色列人啊,

你們要稱頌耶和華!

亞倫的子孫啊,

你們要稱頌耶和華!

20利未的子孫啊,

你們要稱頌耶和華!

你們敬畏耶和華的人都要稱頌祂!135·15-20 平行經文:詩篇115·4-11

21要讚美錫安的耶和華,

讚美住在耶路撒冷的耶和華。

你們要讚美耶和華!