መዝሙር 134 – New Amharic Standard Version NASV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 134:1-3

መዝሙር 134

የሠርክ መዝሙር

መዝሙረ መዓርግ።

1እናንት በሌሊት ቆማችሁ በእግዚአብሔር ቤት የምታገለግሉ፣

የእግዚአብሔር ባሪያዎች ሁላችሁ እግዚአብሔርን ባርኩ።

2በመቅደሱ ውስጥ እጆቻችሁን አንሡ፤

እግዚአብሔርንም ባርኩ።

3ሰማይንና ምድርን የሠራ እግዚአብሔር

ከጽዮን ይባርክህ።