መዝሙር 133 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 133:1-3

መዝሙር 133

የወንድማማች ፍቅር

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1ወንድሞች ተስማምተው በአንድነት ሲኖሩ፣

እንዴት መልካም ነው! ምንኛስ ደስ ያሰኛል!

2በራስ ላይ ፈስሶ፣

እስከ ጢም እንደሚዘልቅ፣

እስከ አሮን ጢም እንደሚወርድ፣

እስከ ልብሱም ዐንገትጌ እንደሚደርስ ውድ ሽቱ ነው።

3ደግሞም በጽዮን ተራራ ላይ እንደሚወርድ፣

እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፤

በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን፣

ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዟልና።

Het Boek

Psalmen 133:1-3

1Een bedevaartslied van David.

Kijk eens hoe goed en waardevol het is

als broeders in vrede met elkaar omgaan.

2Dat is net zo kostbaar als de olie

waarmee Aäron werd gezalfd

en die van zijn baard af op zijn kleding vloeide.

3Het is net zo kostbaar als de dauw van de berg Hermon

die de bergen van Jeruzalem bevloeit.

Dat is de plaats waaraan de Here zijn zegen verbindt

en het leven tot in eeuwigheid.