መዝሙር 132 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 132:1-18

መዝሙር 132

የክብረ በዓል መዝሙር

132፥8-10 ተጓ ምብ – 2ዜና 6፥41-42

መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ዳዊትን፣

የታገሠውንም መከራ ሁሉ ዐስብ፤

2እርሱ ለእግዚአብሔር ማለ፤

ለያዕቆብም ኀያል አምላክ እንዲህ ሲል ተሳለ፤

3“ወደ ቤቴ አልገባም፤

ዐልጋዬም ላይ አልወጣም፤

4ለዐይኖቼ እንቅልፍን፣

ለሽፋሽፍቶቼም ሸለብታ አልሰጥም፤

5ለእግዚአብሔር ስፍራን፣

ለያዕቆብም ኀያል አምላክ ማደሪያን እስካገኝ ድረስ።”

6እነሆ፤ በኤፍራታ ሰማነው፤

በቂርያትይዓሪም132፥6 አንዳንዶቹ ያዓር ይላሉ። አገኘነው።

7“ወደ ማደሪያው እንግባ፤

እግሮቹ በሚቆሙበት ቦታ እንስገድ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ተነሥ፤

አንተና የኀይልህ ታቦት ወደ ማረፊያህ ስፍራ ሂዱ።

9ካህናትህ ጽድቅን ይልበሱ፤

ቅዱሳንህም እልል ይበሉ።”

10ስለ አገልጋይህ ስለ ዳዊት ስትል፣

የቀባኸውን ሰው አትተወው።

11እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ፤

በማይታጠፍም ቃሉ እንዲህ አለ፤

“ከገዛ ራስህ ፍሬ፣

በዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ።

12ወንዶች ልጆችህ ኪዳኔን፣

የማስተምራቸውንም ምስክርነቴን ቢጠብቁ፣

ልጆቻቸው በዙፋንህ ላይ፣

ለዘላለም ይቀመጣሉ።”

13እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፣

ማደሪያውም ትሆን ዘንድ ወድዷልና እንዲህ አለ፤

14“ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤

ፈልጌአታለሁና በእርሷ እኖራለሁ።

15እጅግ አትረፍርፌ እባርካታለሁ፤

ድኾቿን እንጀራ አጠግባለሁ።

16ለካህናቷ ድነትን አለብሳለሁ፤

ቅዱሳኗም በደስታ ይዘምራሉ።

17“በዚህም ለዳዊት ቀንድ132፥17 እዚህ ላይ ቀንድ የጥንካሬ ትእምርት ሲሆን፣ ንጉሥን ያመለክታል። አበቅላለሁ፤

ለቀባሁትም ሰው መብራት አዘጋጃለሁ።

18ጠላቶቹን ኀፍረት አከናንባቸዋለሁ፤

እርሱ ግን በራሱ ላይ የደፋው ዘውድ ያበራል።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 132:1-18

第 132 篇

求上帝賜福聖殿

上聖殿朝聖之詩。

1耶和華啊,

求你顧念大衛和他所受的一切苦難。

2他曾向你起誓,

雅各的大能者許願說:

3-5「我不為耶和華找到居所,

不為雅各的大能者找到安居之處,

必不進家門,

不沾床,不睡覺,不打盹。」

6我們在以法他聽到約櫃的消息,

基列·耶琳找到了它。

7讓我們進入耶和華的居所,

在祂腳前俯伏敬拜。

8耶和華啊,

求你起來和你大能的約櫃一同進入聖所。

9願你的祭司身披公義,

願你忠心的子民高聲歡唱。

10為了你僕人大衛的緣故,

求你不要棄絕你所膏立的人。

11耶和華曾向大衛起了永不廢棄的誓說:

「我必使你的後代繼承你的王位。

12你的後代若守我的約,

遵行我教導他們的法度,

他們的子孫必永遠坐在你的寶座上。」

13因為耶和華已經揀選了錫安

願意將錫安作為祂的居所。

14祂說:「這是我永遠的居所;

我要住在這裡,

因為我喜愛這地方。

15我要使她糧食充足,

使她裡面的窮人飲食無憂。

16我要用救恩作她祭司的衣裳,

城裡忠心的子民必高聲歡唱。

17我必使大衛的後裔在那裡做王,

我必為我所膏立的預備明燈。

18我必使他的仇敵滿面羞愧,

但他頭上的王冠必光芒四射。」