መዝሙር 13 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 13:1-6

መዝሙር 13

በአምላኩ የታመነ ሰው አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ?

ፊትህንስ ከእኔ የምትሰውረው እስከ መቼ ድረስ ነው?

2ከሐሳቤ ጋር የምሟገተው፣

ልቤም ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው?

ጠላቴስ በእኔ ላይ የሚያይለው እስከ መቼ ድረስ ነው?

3እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ተመልከት፤

ስማኝም፤

የሞት እንቅልፍ እንዳልተኛ ዐይኖቼን አብራ፤

4በዚህም ጠላቴ፣ “አሸነፍሁት” እንዳይል፣

ባላጋራዎቼም በውድቀቴ ደስ እንዳይላቸው ርዳኝ።

5እኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤

ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።

6ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣

ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ።

Ketab El Hayat

مزمور 13:1-6

الْمَزْمُورُ الثَّالِثَ عَشَرَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1إِلَى مَتَى يَا رَبُّ تَنْسَانِي؟ أَإِلَى الأَبَدِ؟ إِلَى مَتَى تَحْجُبُ وَجْهَكَ عَنِّي؟ 2إِلَى مَتَى أَرْعَى هُمُوماً فِي نَفْسِي وَحُزْناً فِي قَلْبِي كُلَّ يَوْمٍ؟ إِلَى مَتَى يَتَشَامَخُ عَدُوِّي عَلَيَّ؟ 3انْظُرْ إِلَيَّ أَيُّهَا الرَّبُّ إِلَهِى وَاسْتَجِبْ لِي. أَنِرْ عَيْنَيَّ لِئَلّا أَنَامَ نَوْمَةَ الْمَوْتِ، 4فَيَقُولَ عَدُوِّي: قَدْ قَهَرْتُهُ؛ وَيَبْتَهِجَ خُصُومِي بِسُقُوطِي. 5غَيْرَ أَنِّي تَوَكَّلْتُ عَلَى رَحْمَتِكَ، فَيَبْتَهِجُ قَلْبِي حَقّاً بِخَلاصِكَ. 6أُرَنِّمُ لِلرَّبِّ لأَنَّهُ غَمَرَنِي بِإِحْسَانِهِ الْعَمِيمِ.