መዝሙር 13 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 13:1-6

መዝሙር 13

በአምላኩ የታመነ ሰው አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ?

ፊትህንስ ከእኔ የምትሰውረው እስከ መቼ ድረስ ነው?

2ከሐሳቤ ጋር የምሟገተው፣

ልቤም ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው?

ጠላቴስ በእኔ ላይ የሚያይለው እስከ መቼ ድረስ ነው?

3እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ተመልከት፤

ስማኝም፤

የሞት እንቅልፍ እንዳልተኛ ዐይኖቼን አብራ፤

4በዚህም ጠላቴ፣ “አሸነፍሁት” እንዳይል፣

ባላጋራዎቼም በውድቀቴ ደስ እንዳይላቸው ርዳኝ።

5እኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤

ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።

6ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣

ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 13:1-6

第 13 篇

祈求上帝垂顧

大衛的詩,交給樂長。

1耶和華啊,你忘記我要到何時呢?要到永遠嗎?

你轉臉不顧我要到何時呢?

2我思緒煩亂,日夜憂傷要到何時呢?

我的仇敵佔盡上風要到何時呢?

3我的上帝耶和華啊,

求你垂顧我,回答我,

使我眼睛明亮,

免得我在沉睡中死去,

4免得我的仇敵說:「我們戰勝了他!」

免得他們因我敗落而歡喜。

5我深信你的慈愛,

我的心要因你的拯救而歡欣。

6耶和華一直恩待我,

我要向祂歌唱。