መዝሙር 127
በእግዚአብሔር መታመን
የሰሎሞን መዝሙረ መዓርግ።
1እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፣
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤
እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፣
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።
2የዕለት ጕርስ ለማግኘት በመጣር፣
ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣
አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤
እርሱ ለሚወድዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።127፥2 ወይም ተኝተው ሳሉ ምግብ ያዘጋጅላቸዋል።
3እነሆ፤ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤
የማሕፀንም ፍሬ ከቸርነቱ የሚገኝ ነው።
4በወጣትነት የተገኙ ወንዶች ልጆች፣
በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው።
5ኰረጆዎቹ በእነዚህ የተሞሉ፣
የተባረከ ሰው ነው፤
ከጠላቶቻቸው ጋር በአደባባይ በሚሟገቱበት ጊዜ፣
አይዋረዱም።
Psalm 127
A song of ascents. Of Solomon.
1Unless the Lord builds the house,
the builders labor in vain.
Unless the Lord watches over the city,
the guards stand watch in vain.
2In vain you rise early
and stay up late,
toiling for food to eat—
for he grants sleep to127:2 Or eat— / for while they sleep he provides for those he loves.
3Children are a heritage from the Lord,
offspring a reward from him.
4Like arrows in the hands of a warrior
are children born in one’s youth.
5Blessed is the man
whose quiver is full of them.
They will not be put to shame
when they contend with their opponents in court.