መዝሙር 127 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 127:1-5

መዝሙር 127

በእግዚአብሔር መታመን

የሰሎሞን መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፣

ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤

እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፣

ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።

2የዕለት ጕርስ ለማግኘት በመጣር፣

ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣

አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤

እርሱ ለሚወድዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።127፥2 ወይም ተኝተው ሳሉ ምግብ ያዘጋጅላቸዋል።

3እነሆ፤ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤

የማሕፀንም ፍሬ ከቸርነቱ የሚገኝ ነው።

4በወጣትነት የተገኙ ወንዶች ልጆች፣

በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው።

5ኰረጆዎቹ በእነዚህ የተሞሉ፣

የተባረከ ሰው ነው፤

ከጠላቶቻቸው ጋር በአደባባይ በሚሟገቱበት ጊዜ፣

አይዋረዱም።

Korean Living Bible

시편 127:1-5

헛된 수고와 하나님의 축복

(솔로몬의 시. 성전에 올라가는 노래)

1여호와께서

집을 세우지 않으시면

건축자들의 수고가 헛되고

여호와께서

성을 지키지 않으시면

파수병이 보초를 서도 헛일이다.

2아침 일찍 일어나고

밤 늦게 자면서

고달프게 벌어 먹고 사는 것도

헛된 일이다.

그래서 여호와께서는

자기가 사랑하는 자에게

잠을 주신다.

3자녀는 여호와께서 주신 127:3 또는 ‘기업이며’선물이며

상급으로 주신 그의 축복이다.

4젊었을 때 낳은 자식은

용사의 손 안에 있는 화살 같아서

5그런 화살이 많은 사람은 행복하다.

그가 3법정에서

자기 원수를 만나도

수치를 당하지 않으리라.