መዝሙር 123 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 123:1-4

መዝሙር 123

የተጨነቀ ሰው ጸሎት

መዝሙረ መዓርግ።

1በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጥህ ሆይ፤

ዐይኖቼን ወደ አንተ አነሣለሁ።

2የባሪያዎች ዐይን ወደ ጌታቸው እጅ፣

የባሪያዪቱም ዐይን ወደ እመቤቷ እጅ እንደሚመለከት፣

ምሕረት እስከሚያደርግልን ድረስ፣

የእኛም ዐይኖች ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ይመለከታሉ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ንቀት በዝቶብናልና፣

ማረን፤ እባክህ ማረን።

4ነፍሳችን የቅንጡዎች ስድብ፣

የትዕቢተኞችም ንቀት እጅግ በዝቶባታል።

New International Version

Psalms 123:1-4

Psalm 123

A song of ascents.

1I lift up my eyes to you,

to you who sit enthroned in heaven.

2As the eyes of slaves look to the hand of their master,

as the eyes of a female slave look to the hand of her mistress,

so our eyes look to the Lord our God,

till he shows us his mercy.

3Have mercy on us, Lord, have mercy on us,

for we have endured no end of contempt.

4We have endured no end

of ridicule from the arrogant,

of contempt from the proud.