መዝሙር 123 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 123:1-4

መዝሙር 123

የተጨነቀ ሰው ጸሎት

መዝሙረ መዓርግ።

1በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጥህ ሆይ፤

ዐይኖቼን ወደ አንተ አነሣለሁ።

2የባሪያዎች ዐይን ወደ ጌታቸው እጅ፣

የባሪያዪቱም ዐይን ወደ እመቤቷ እጅ እንደሚመለከት፣

ምሕረት እስከሚያደርግልን ድረስ፣

የእኛም ዐይኖች ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ይመለከታሉ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ንቀት በዝቶብናልና፣

ማረን፤ እባክህ ማረን።

4ነፍሳችን የቅንጡዎች ስድብ፣

የትዕቢተኞችም ንቀት እጅግ በዝቶባታል።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 123:1-4

第 123 篇

祈求上帝憐憫

上聖殿朝聖之詩。

1在天上做王的耶和華啊!

我仰望你。

2我們要仰望我們的上帝耶和華,

如同僕人仰望主人、婢女仰望主母,

一直到蒙祂憐憫。

3耶和華啊,

求你憐憫我們,求你憐憫我們,

因為我們飽受鄙視。

4我們飽受富足人的嘲弄、驕傲人的鄙視。