መዝሙር 122 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 122:1-9

መዝሙር 122

ኢየሩሳሌም እልል በዪ!

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ”

ባሉኝ ጊዜ፣ ደስ አለኝ።

2ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግሮቻችን ከደጅሽ ውስጥ ቆመዋል።

3ኢየሩሳሌም እጅግ እንደ ተጠጋጋች፣

ከተማ ሆና ተሠርታለች።

4ለእስራኤል በተሰጠው ሥርዐት መሠረት፣

የእግዚአብሔርን ስም ለማመስገን፣

የእግዚአብሔር ነገዶች

ወደዚያ ይመጣሉ።

5በዚያም የፍርድ ዙፋኖች የሆኑት፣

የዳዊት ቤት ዙፋኖች ተዘርግተዋል።

6እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤

“የሚወድዱሽ ይለምልሙ፤

7በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤

በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”።

8ስለ ወንድሞቼና ስለ ባልንጀሮቼ፣

“በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።

9ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት፣

በጎነትሽን እሻለሁ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 122:1-9

122

1エルサレムの主の宮に行こうと

誘われた時のうれしさは忘れられません。

2-3私たちは今、都の雑踏の中に立っています。

4神のおきてに従って、

イスラエル中の主の民がここに集まり、

主を礼拝し、感謝と賛美をささげるのです。

5都の門のそばでは、

裁判官が人々の論争を裁いています。

6エルサレムの平和のために祈ってください。

この都を愛する人々に繁栄がもたらされますように。

7エルサレムの城壁のうちに平和がみなぎり、

宮殿は富み栄えますように。

8この都に住む友、兄弟のために願います。

9主の宮にふさわしい平和で満たされますようにと。