መዝሙር 122 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 122:1-9

መዝሙር 122

ኢየሩሳሌም እልል በዪ!

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ”

ባሉኝ ጊዜ፣ ደስ አለኝ።

2ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግሮቻችን ከደጅሽ ውስጥ ቆመዋል።

3ኢየሩሳሌም እጅግ እንደ ተጠጋጋች፣

ከተማ ሆና ተሠርታለች።

4ለእስራኤል በተሰጠው ሥርዐት መሠረት፣

የእግዚአብሔርን ስም ለማመስገን፣

የእግዚአብሔር ነገዶች

ወደዚያ ይመጣሉ።

5በዚያም የፍርድ ዙፋኖች የሆኑት፣

የዳዊት ቤት ዙፋኖች ተዘርግተዋል።

6እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤

“የሚወድዱሽ ይለምልሙ፤

7በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤

በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”።

8ስለ ወንድሞቼና ስለ ባልንጀሮቼ፣

“በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።

9ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት፣

በጎነትሽን እሻለሁ።

Священное Писание

Забур 122:1-4

Песнь 122

Песнь восхождения.

1К Тебе поднимаю глаза свои,

Обитающий на небесах!

2Как глаза слуг смотрят на руку своего господина

и глаза служанки – на руку своей госпожи,

так наши глаза обращены на Вечного,

до тех пор, пока Он не смилуется над нами.

3Помилуй нас, Вечный, помилуй нас,

потому что мы долго терпели презрение.

4Долго мы терпели оскорбление от надменных

и презрение от гордых.