መዝሙር 121
የእስራኤል ጠባቂ
መዝሙረ መዓርግ።
1ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤
ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል?
2ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣
ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል።
3እግርህ እንዲሸራተት አይፈቅድም፤
የሚጠብቅህም አይተኛም።
4እነሆ፤ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም፤ አያንቀላፋምም።
5እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፤
እግዚአብሔር በቀኝህ በኩል ይከልልሃል።
6ፀሓይ በቀን አያቃጥልህም፤
ጨረቃም በሌሊት ጕዳት አታመጣብህም።
7እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፤
ነፍስህንም ይንከባከባታል።
8እግዚአብሔር ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣
መውጣትህንና መግባትህን ይጠብቃል።