መዝሙር 119 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 119:1-176

መዝሙር 119119 የዚህ መዝሙር የግጥም ስንኞች መነሻ ወይም መነሻና መድረሻ ሆህያት ቍልቍል ሲነበቡ ትርጕም ዐዘል ናቸው። እያንዳንዱ ስንኝ ተመሳሳይ በሆነ በዕብራይስጥ ፊደል ይጀምራል።

ውዳሴ ለሕገ እግዚአብሔር

א አሌፍ

1መንገዳቸው ነቀፋ የሌለበት፣

በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው።

2ምስክርነቱን የሚጠብቁ፣

በፍጹምም ልብ የሚሹት የተባረኩ ናቸው፤

3ዐመፅን አያደርጉም፤

ነገር ግን በመንገዱ ይሄዳሉ።

4ጠንቅቀን እንጠብቃት ዘንድ፣

አንተ ሥርዐትን አዝዘሃል።

5ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ፣

ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ!

6ወደ ትእዛዞችህ ስመለከት፣

በዚያን ጊዜ አላፍርም።

7የጽድቅ ፍርድህን ስማር፣

በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ።

8ሥርዐትህን እጠብቃለሁ፤

ፈጽመህ አትተወኝ።

ב ቤት

9ጕልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል?

በቃልህ መሠረት በመኖር ነው።

10በሙሉ ልቤ ፈለግሁህ፤

ከትእዛዞችህ ፈቀቅ እንዳልል አድርገኝ።

11አንተን እንዳልበድል፣

ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ቡሩክ ነህ፤

ሥርዐትህን አስተምረኝ።

13ከአንደበትህ የሚወጣውን ደንብ ሁሉ፣

በከንፈሬ እናገራለሁ።

14ሰው በሀብቱ ብዛት ደስ እንደሚለው፣

ምስክርነትህን በመከተል ደስ ይለኛል።

15ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤

ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ።

16በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤

ቃልህንም አልዘነጋም።

ג ጊሜል

17ሕያው እንድሆን፣ ቃልህንም እንድጠብቅ፣

ለአገልጋይህ መልካም አድርግ።

18ከሕግህ ድንቅ ነገርን እንዳይ፣

ዐይኖቼን ክፈት።

19እኔ በምድር ላይ መጻተኛ ነኝ፤

ትእዛዞችህን ከእኔ አትሰውር።

20ዘወትር ደንብህን በመናፈቅ፣

ነፍሴ እጅግ ዛለች።

21ከትእዛዞችህ የሳቱትን፣

እብሪተኞችንና ርጉሞችን ትገሥጻለህ።

22ምስክርነትህን ጠብቄአለሁና፣

ስድብንና ንቀትን ከእኔ አርቅ።

23ገዦች ተቀምጠው ቢዶልቱብኝ እንኳ፣

አገልጋይህ ሥርዐትህን ያሰላስላል።

24ምስክርነትህ ለእኔ ደስታዬ ነው፤

መካሪዬም ነው።

ד ዳሌት

25ነፍሴ ከዐፈር ተጣበቀች፤

እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።

26ስለ መንገዴ ገልጬ ነገርሁህ፤ አንተም መለስህልኝ፤

ሥርዐትህን አስተምረኝ።

27የድንጋጌህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፤

እኔም ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ።

28ነፍሴ በሐዘን ተዝለፈለፈች፤

እንደ ቃልህ አበርታኝ።

29የሽንገላን መንገድ ከእኔ አርቅ፤

ሕግህን በጸጋህ ስጠኝ።

30የእውነትን መንገድ መርጫለሁ፤

ሕግህንም ፊት ለፊቴ አድርጌአለሁ።

31እግዚአብሔር ሆይ፤ ከምስክርነትህ ጋር ተጣብቄአለሁ፤

አሳልፈህ ለውርደት አትስጠኝ።

32ልቤን አስፍተህልኛልና፣

በትእዛዞችህ መንገድ እሮጣለሁ።

ה ሄ

33እግዚአብሔር ሆይ፤ የሥርዐትህን መንገድ አስተምረኝ፤

እኔም እስከ መጨረሻው እጠብቀዋለሁ።

34ሕግህን እንድጠብቅ፣ በፍጹም ልቤም እንድታዘዘው፣ ማስተዋልን ስጠኝ።

35በእርሷ ደስ ይለኛልና፣

በትእዛዝህ መንገድ ምራኝ።

36ከራስ ጥቅም ይልቅ፣

ልቤን ወደ ምስክርነትህ አዘንብል።

37ከንቱ ነገር ከማየት ዐይኖቼን መልስ፤

በራስህ መንገድ119፥37 አንዳንድ ትርጕሞች እንደ ቃልህ ይላሉ። እንደ ገና ሕያው አድርገኝ።

38ትፈራ ዘንድ፣

ለአገልጋይህ የገባኸውን ቃል ፈጽም።

39የምፈራውን መዋረድ ከእኔ አርቅ፤

ደንብህ መልካም ነውና።

40እነሆ፤ ድንጋጌህን ናፈቅሁ፤

በጽድቅህ ሕያው አድርገኝ።

ו ዋው

41እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ወደ እኔ ይምጣ፤

ማዳንህም እንደ ቃልህ ይላክልኝ።

42በቃልህ ታምኛለሁና፣

ለሚሰድቡኝ መልስ እሰጣለሁ።

43ሕግህን ተስፋ አድርጌአለሁና፣

የእውነትን ቃል ከአፌ ፈጽመህ አታርቅ።

44ከዘላለም እስከ ዘላለም፣

ሕግህን ዘወትር እጠብቃለሁ።

45ሥርዐትህን እሻለሁና፣

እንደ ልቤ ወዲያ ወዲህ እመላለሳለሁ።

46ምስክርነትህን በነገሥታት ፊት እናገራለሁ፤

ይህን በማድረግም ዕፍረት አይሰማኝም።

47እኔ እወድደዋለሁና፣

በትእዛዝህ ደስ ይለኛል።

48እጆቼን ወደምወዳቸው119፥48 ወይም ለምወድዳቸው ትእዛዞችህ አነሣለሁ፤

ሥርዐትህንም አሰላስላለሁ።

ז ዛይን

49ለአገልጋይህ የገባኸውን ቃል ዐስብ፤

በዚያ ተስፋ ሰጥተኸዋልና።

50ቃልህ ሕያው ያደርገኛልና፣

ይህች በመከራዬ መጽናኛዬ ናት።

51እብሪተኞች እጅግ ተሣለቁብኝ፤

እኔ ግን ከሕግህ ንቅንቅ አልልም።

52እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጥንት የነበረውን ድንጋጌህን አሰብሁ፤ በዚህም ተጽናናሁ።

53ሕግህን ከተዉ ክፉዎች የተነሣ፣

ቍጣ ወረረኝ።

54በእንግድነቴ አገር፣

ሥርዐትህ መዝሙሬ ናት።

55እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህን በሌሊት ዐስባለሁ፤

ሕግህንም እጠብቃለሁ።

56ሥርዐትህን እከተላለሁ፤

ይህችም ተግባሬ ሆነች።

ח ኼት

57እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤

ቃልህን ለመታዘዝ ቈርጫለሁ።

58በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤

እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ።

59መንገዴን ቃኘሁ፤

አካሄዴንም ወደ ምስክርህ አቀናሁ።

60ትእዛዝህን ለመጠበቅ፣

ቸኰልሁ፤ አልዘገየሁምም።

61የክፉዎች ገመድ ተተበተበብኝ፤ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም።

62ስለ ጻድቅ ሥርዐትህ፣

በእኩለ ሌሊት ላመሰግንህ እነሣለሁ።

63እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፣

ሥርዐትህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ።

64እግዚአብሔር ሆይ፤ ምድር በምሕረትህ ተሞላች፤

ሥርዐትህን አስተምረኝ።

ט ቴት

65እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቃልህ፣

ለአገልጋይህ በጎ ውለሃል።

66በትእዛዞችህ አምናለሁና፣

በጎ ማስተዋልንና ዕውቀትን አስተምረኝ።

67እንዲያው ሳይቸግረኝ መንገድ ስቼ ሄድሁ፤

አሁን ግን ቃልህን እጠብቃለሁ።

68አንተ መልካም ነህ፤ የምታደርገው መልካም ነው፤

እንግዲህ ሥርዐትህን አስተምረኝ።

69እብሪተኞች ስሜን በሐሰት አጠፉ፤

እኔ ግን ትእዛዝህን በፍጹም ልብ እጠብቃለሁ።

70ልባቸው የሠባና የደነደነ ነው፤

እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል።

71ሥርዐትህን እማር ዘንድ፣

በመከራ ውስጥ ማለፌ መልካም ሆነልኝ።

72ከአእላፋት ብርና ወርቅ ይልቅ፣

ከአፍህ የሚወጣው ሕግ ይሻለኛል።

י ዮድ

73እጆችህ ሠሩኝ፤ አበጃጁኝም፤

ትእዛዞችህን እንድማር ማስተዋልን ስጠኝ።

74ቃልህን ተስፋ አድርጌአለሁና፣

የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይበላቸው።

75እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍርድህ የጽድቅ ፍርድ፣

ያስጨነቅኸኝም በታማኝነት እንደ ሆነ ዐወቅሁ።

76ለአገልጋይህ በገባኸው ቃል መሠረት፣

ምሕረትህ ለመጽናናት ትሁነኝ።

77ሕግህ ደስታዬ ነውና፣

በሕይወት እኖር ዘንድ ቸርነትህ ትምጣልኝ።

78እብሪተኞች ያለ ምክንያት በደል አድርሰውብኛልና ይፈሩ፤

እኔ ግን ትእዛዞችህን አሰላስላለሁ።

79አንተን የሚፈሩህ፣

ምስክርነትህንም የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ።

80እኔ እንዳላፍር፣ ልቤ በሥርዐትህ ፍጹም ይሁን።

כ ካፍ

81ነፍሴ ማዳንህን እጅግ ናፈቀች፤

ቃልህንም ተስፋ አደርጋለሁ።

82“መቼ ታጽናናኛለህ?” እያልሁ፣

ዐይኖቼ ቃልህን በመጠባበቅ ደከሙ።

83ጢስ የጠጣ የወይን አቍማዳ ብመስልም፣

ሥርዐትህን አልረሳሁም።

84የባሪያህ ዕድሜ ስንት ቢሆን ነው?

ታዲያ፣ በሚያሳድዱኝ ላይ የምትፈርደው መቼ ይሆን?

85በሕግህ መሠረት የማይሄዱ እብሪተኞች

ማጥመጃ ጕድጓድ ቈፈሩልኝ።

86ትእዛዞችህ ሁሉ አስተማማኝ ናቸው፤

ሰዎች ያለ ምክንያት አሳድደውኛልና ርዳኝ።

87ከምድር ላይ ሊያስወግዱኝ ጥቂት ቀራቸው፤

እኔ ግን ትእዛዞችህን አልተውሁም።

88እንደ ምሕረትህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ፤

እኔም የአፍህን ምስክርነት እጠብቃለሁ።

ל ላሜድ

89እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃልህ በሰማይ፣

ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

90ታማኝነትህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ሁሉ ይኖራል፤

ምድርን መሠረትሃት፤ እርሷም ጸንታ ትኖራለች።

91ሁሉም አገልጋይህ ነውና፣

በሕግህ መሠረት እስከ ዛሬ ድረስ ጸንተው ይኖራሉ።

92ሕግህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ፣

በመከራዬ ወቅት በጠፋሁ ነበር።

93በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና፣

ትእዛዝህን ከቶ አልረሳም።

94እኔ የአንተ ነኝ፤ እባክህ አድነኝ፤

ሕግህንም ፈልጌአለሁና።

95ክፉዎች ሊያጠፉኝ አድብተዋል፤

እኔ ግን ምስክርነትህን አሰላስላለሁ።

96ለፍጹምነት ሁሉ ዳርቻ እንዳለው አየሁ፤

ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው።

מ ሜም

97አቤቱ፤ ሕግህን ምንኛ ወደድሁ!

ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ።

98ትእዛዞችህ ምንጊዜም ስለማይለዩኝ፣

ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረጉኝ።

99ምስክርነትህን አሰላስላለሁና፣

ከአስተማሪዎቼ ሁሉ የላቀ አስተዋይ ልብ አገኘሁ።

100መመሪያህን ተከትዬ እሄዳለሁና፣

ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋይ ሆንሁ።

101ቃልህን እጠብቅ ዘንድ፣

እግሬን ከክፉ መንገድ ሁሉ ከለከልሁ።

102አንተው ራስህ አስተምረኸኛልና፣

ከድንጋጌህ ዘወር አላልሁም።

103ቃልህ ለምላሴ ምንኛ ጣፋጭ ነው!

ለአፌም ከማር ወለላ ይልቅ ጣዕም አለው።

104ከመመሪያህ ማስተዋልን አገኘሁ፤

ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ።

נ ኑን

105ሕግህ ለእግሬ መብራት፣

ለመንገዴም ብርሃን ነው።

106የጽድቅ ሕግህን ለመጠበቅ፤

ምያለሁ፤ ይህንኑ አጸናለሁ።

107እጅግ ተቸግሬአለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።

108እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈቅጄ ያቀረብሁትን የአፌን የምስጋና መሥዋዕት ተቀበል፤

ሕግህንም አስተምረኝ።

109ነፍሴ ዘወትር አደጋ ላይ ናት፤

ሕግህን ግን አልረሳሁም።

110ክፉዎች ወጥመድ ዘረጉብኝ፤

እኔ ግን መመሪያህን አልተላለፍሁም።

111ምስክርነትህ የዘላለም ውርሴ ናት፤

ልቤ በዚህ ሐሤት ያደርጋልና።

112ትእዛዝህን ለዘላለም፣ እስከ ወዲያኛው ለመፈጸም፣

ልቤን ወደዚያው አዘነበልሁ።

ס ሳሜክ

113መንታ ልብ ያላቸውን ጠላሁ፤

ሕግህን ግን ወደድሁ።

114አንተ መጠጊያዬና ጋሻዬ ነህ፤

ቃልህን በተስፋ እጠብቃለሁ።

115የአምላኬን ትእዛዞች እጠብቅ ዘንድ፣

እናንት ክፉ አድራጊዎች ከእኔ ራቁ።

116እንደ ቃልህ ደግፈኝ፤ እኔም ሕያው እሆናለሁ፤

ተስፋዬም መና ቀርቶ አልፈር።

117ያለ ሥጋት እቀመጥ ዘንድ ደግፈህ ያዘኝ፤

ሥርዐትህንም ዘወትር እመለከታለሁ።

118መሠሪነታቸው በከንቱ ነውና፣

ከሥርዐትህ ውጭ የሚሄዱትን ሁሉ ወዲያ አስወገድሃቸው።

119የምድርን ክፉዎች ሁሉ እንደ ጥራጊ አስወገድሃቸው፤

ስለዚህ ምስክርህን ወደድሁ።

120ሥጋዬ አንተን በመፍራት ይንቀጠቀጣል፤

ፍርድህንም እፈራለሁ።

ע ዐዪን

121ፍትሕና ጽድቅ ያለበትን ሠርቻለሁ፤

ለሚጨቍኑኝ አሳልፈህ አትስጠኝ።

122ለባሪያህ በጎነት ዋስትና ሁን፤

እብሪተኞች እንዲጨቍኑኝ አትፍቀድላቸው።

123ዐይኖቼ ማዳንህን፣

የጽድቅ ቃልህን በመጠባበቅ ደከሙ።

124ለባሪያህ እንደ ምሕረትህ መጠን አድርግ፤

ሥርዐትህንም አስተምረኝ።

125እኔ ባሪያህ ነኝ፤

ምስክርነትህን ዐውቅ ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ።

126እግዚአብሔር ሆይ፤

ሕግህ እየተጣሰ ነውና፣

ጊዜው አንተ የምትሠራበት ነው።

127ስለዚህ ከወርቅ፣ ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ፣

ትእዛዞችህን ወደድሁ።

128መመሪያህ ሙሉ በሙሉ ልክ ነው አልሁ፤

ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ።

פ ፔ

129ምስክርነትህ ሁሉ ድንቅ ነው፤

ስለዚህ ነፍሴ ትጠብቀዋለች።

130የቃልህ ትርጓሜ ያበራል፤

አላዋቂዎችንም አስተዋዮች ያደርጋል።

131ትእዛዝህን ናፍቄአለሁና፣

አፌን ከፈትሁ፤ አለከለክሁም።

132ስምህን ለሚወድዱ ማድረግ ልማድህ እንደ ሆነ ሁሉ፣

ወደ እኔ ተመልሰህ ምሕረት አድርግልኝ።

133አካሄዴን እንደ ቃልህ ቀና አድርግልኝ፤

ኀጢአትም በላዬ እንዲሠለጥን አትፍቀድ።

134ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል፣

ከሰዎች ጥቃት ታደገኝ።

135በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤

ሥርዐትህንም አስተምረኝ።

136ሕግህ ባለመከበሩ፤

እንባዬ እንደ ውሃ ይፈስሳል።

צ ጻዴ

137እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤

ፍርድህም ትክክል ነው።

138ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤

እጅግ አስተማማኝም ነው።

139ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣

ቅናት አሳረረኝ።

140ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤

ባሪያህም ወደደው።

141እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ፤

ነገር ግን መመሪያህን አልዘነጋሁም።

142ጽድቅህ ዘላለማዊ ጽድቅ ነው፤

ሕግህም እውነት ነው።

143መከራና ሥቃይ ደርሶብኛል፤

ነገር ግን ትእዛዝህ ደስታዬ ነው።

144ምስክርነትህ ለዘላለም የጽድቅ ምስክርነት ነው፤

በሕይወት እኖር ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ።

ק ቆፍ

145እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ እጮኻለሁና መልስልኝ፤

ሥርዐትህንም እጠብቃለሁ።

146ወደ አንተ እጣራለሁና አድነኝ፤

ምስክርነትህንም እጠብቃለሁ።

147ትረዳኝ ዘንድ ጎሕ ሳይቀድድ ተነሥቼ እጮኻለሁ፤

ቃልህንም ተስፋ አደርጋለሁ።

148ቃልህን አሰላስል ዘንድ፣

ዐይኔ ሌሊቱን ሙሉ ሳይከደን ያድራል።

149እንደ ቸርነትህ መጠን ድምፄን ስማ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ሕግህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።

150ደባ የሚያውጠነጥኑ ወደ እኔ ቀርበዋል፤

ከሕግህ ግን የራቁ ናቸው።

151እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ቅርብ ነህ፤

ትእዛዞችህም ሁሉ እውነት ናቸው።

152ለዘላለም እንደ መሠረትሃቸው፣

ከጥንት ምስክርነትህ ተረድቻለሁ።

ר ሬሽ

153ሕግህን አልረሳሁምና፣ ሥቃዬን ተመልከት፤ ታደገኝም።

154ተሟገትልኝ፤ አድነኝም፤

እንደ ቃልህም ሕያው አድርገኝ።

155ሥርዐትህን ስለማይሹ፣

ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው።

156እግዚአብሔር ሆይ፤ ርኅራኄህ ታላቅ ነው፤

እንደ ሕግህ ሕያው አድርገኝ።

157የሚያሳድዱኝ ጠላቶቼ ብዙዎች ናቸው፤

እኔ ግን ከምስክርህ ዘወር አላልሁም።

158ቃልህን አይጠብቁምና፣

ከዳተኞችን አይቼ አርቃቸዋለሁ።

159መመሪያህን እንዴት እንደምወድድ ተመልከት፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ።

160ቃልህ በሙሉ እውነት ነው፤

ጻድቅ የሆነው ሕግህም ዘላለማዊ ነው።

ש ሲን እና ሺን

161ገዦች ያለ ምክንያት አሳደዱኝ፤

ልቤ ግን ከቃልህ የተነሣ እጅግ ፈራ።

162ትልቅ ምርኮ እንዳገኘ ሰው፣

በቃልህ ደስ አለኝ።

163ሐሰትን እጠላለሁ፤ እጸየፋለሁ፤

ሕግህን ግን ወደድሁ።

164ጻድቅ ስለ ሆነው ሕግህ፣

በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለሁ።

165ሕግህን የሚወድዱ ብዙ ሰላም አላቸው፤

ዕንቅፋትም የለባቸውም።

166እግዚአብሔር ሆይ፤ ማዳንህን ተስፋ አደርጋለሁ፤

ትእዛዝህንም እፈጽማለሁ።

167ነፍሴ ምስክርነትህን ትጠብቃለች፤

እጅግ እወድደዋለሁና።

168መንገዴ ሁሉ በፊትህ ግልጽ ነውና፣

ሕግህንና ምስክርነትህን እጠብቃለሁ።

ת ታው

169እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴ ከፊትህ ይድረስ፤

እንደ ቃልህም ማስተዋልን ስጠኝ።

170ልመናዬ ከፊትህ ይድረስ፤

እንደ ቃልህም ታደገኝ።

171ሥርዐትህን አስተምረኸኛልና፣

ከንፈሮቼ ምስጋናን አፈለቁ።

172ትእዛዞችህ ሁሉ የጽድቅ ትእዛዞች ናቸውና፣

አንደበቴ ስለ ቃልህ ይዘምር።

173ትእዛዝህን መርጫለሁና፣

እጅህ እኔን ለመርዳት ዝግጁ ይሁን።

174እግዚአብሔር ሆይ፤ ማዳንህን ናፈቅሁ፤

ሕግህም ደስታዬ ነው።

175አመሰግንህ ዘንድ በሕይወት ልኑር፤

ሕግህም ይርዳኝ።

176እንደ ጠፋ በግ ተቅበዘበዝሁ፤

ትእዛዞችህን አልረሳሁምና፣

ባሪያህን ፈልገው።

New International Version

Psalms 119:1-176

Psalm 119119 This psalm is an acrostic poem, the stanzas of which begin with successive letters of the Hebrew alphabet; moreover, the verses of each stanza begin with the same letter of the Hebrew alphabet.

א Aleph

1Blessed are those whose ways are blameless,

who walk according to the law of the Lord.

2Blessed are those who keep his statutes

and seek him with all their heart—

3they do no wrong

but follow his ways.

4You have laid down precepts

that are to be fully obeyed.

5Oh, that my ways were steadfast

in obeying your decrees!

6Then I would not be put to shame

when I consider all your commands.

7I will praise you with an upright heart

as I learn your righteous laws.

8I will obey your decrees;

do not utterly forsake me.

ב Beth

9How can a young person stay on the path of purity?

By living according to your word.

10I seek you with all my heart;

do not let me stray from your commands.

11I have hidden your word in my heart

that I might not sin against you.

12Praise be to you, Lord;

teach me your decrees.

13With my lips I recount

all the laws that come from your mouth.

14I rejoice in following your statutes

as one rejoices in great riches.

15I meditate on your precepts

and consider your ways.

16I delight in your decrees;

I will not neglect your word.

ג Gimel

17Be good to your servant while I live,

that I may obey your word.

18Open my eyes that I may see

wonderful things in your law.

19I am a stranger on earth;

do not hide your commands from me.

20My soul is consumed with longing

for your laws at all times.

21You rebuke the arrogant, who are accursed,

those who stray from your commands.

22Remove from me their scorn and contempt,

for I keep your statutes.

23Though rulers sit together and slander me,

your servant will meditate on your decrees.

24Your statutes are my delight;

they are my counselors.

ד Daleth

25I am laid low in the dust;

preserve my life according to your word.

26I gave an account of my ways and you answered me;

teach me your decrees.

27Cause me to understand the way of your precepts,

that I may meditate on your wonderful deeds.

28My soul is weary with sorrow;

strengthen me according to your word.

29Keep me from deceitful ways;

be gracious to me and teach me your law.

30I have chosen the way of faithfulness;

I have set my heart on your laws.

31I hold fast to your statutes, Lord;

do not let me be put to shame.

32I run in the path of your commands,

for you have broadened my understanding.

ה He

33Teach me, Lord, the way of your decrees,

that I may follow it to the end.119:33 Or follow it for its reward

34Give me understanding, so that I may keep your law

and obey it with all my heart.

35Direct me in the path of your commands,

for there I find delight.

36Turn my heart toward your statutes

and not toward selfish gain.

37Turn my eyes away from worthless things;

preserve my life according to your word.119:37 Two manuscripts of the Masoretic Text and Dead Sea Scrolls; most manuscripts of the Masoretic Text life in your way

38Fulfill your promise to your servant,

so that you may be feared.

39Take away the disgrace I dread,

for your laws are good.

40How I long for your precepts!

In your righteousness preserve my life.

ו Waw

41May your unfailing love come to me, Lord,

your salvation, according to your promise;

42then I can answer anyone who taunts me,

for I trust in your word.

43Never take your word of truth from my mouth,

for I have put my hope in your laws.

44I will always obey your law,

for ever and ever.

45I will walk about in freedom,

for I have sought out your precepts.

46I will speak of your statutes before kings

and will not be put to shame,

47for I delight in your commands

because I love them.

48I reach out for your commands, which I love,

that I may meditate on your decrees.

ז Zayin

49Remember your word to your servant,

for you have given me hope.

50My comfort in my suffering is this:

Your promise preserves my life.

51The arrogant mock me unmercifully,

but I do not turn from your law.

52I remember, Lord, your ancient laws,

and I find comfort in them.

53Indignation grips me because of the wicked,

who have forsaken your law.

54Your decrees are the theme of my song

wherever I lodge.

55In the night, Lord, I remember your name,

that I may keep your law.

56This has been my practice:

I obey your precepts.

ח Heth

57You are my portion, Lord;

I have promised to obey your words.

58I have sought your face with all my heart;

be gracious to me according to your promise.

59I have considered my ways

and have turned my steps to your statutes.

60I will hasten and not delay

to obey your commands.

61Though the wicked bind me with ropes,

I will not forget your law.

62At midnight I rise to give you thanks

for your righteous laws.

63I am a friend to all who fear you,

to all who follow your precepts.

64The earth is filled with your love, Lord;

teach me your decrees.

ט Teth

65Do good to your servant

according to your word, Lord.

66Teach me knowledge and good judgment,

for I trust your commands.

67Before I was afflicted I went astray,

but now I obey your word.

68You are good, and what you do is good;

teach me your decrees.

69Though the arrogant have smeared me with lies,

I keep your precepts with all my heart.

70Their hearts are callous and unfeeling,

but I delight in your law.

71It was good for me to be afflicted

so that I might learn your decrees.

72The law from your mouth is more precious to me

than thousands of pieces of silver and gold.

י Yodh

73Your hands made me and formed me;

give me understanding to learn your commands.

74May those who fear you rejoice when they see me,

for I have put my hope in your word.

75I know, Lord, that your laws are righteous,

and that in faithfulness you have afflicted me.

76May your unfailing love be my comfort,

according to your promise to your servant.

77Let your compassion come to me that I may live,

for your law is my delight.

78May the arrogant be put to shame for wronging me without cause;

but I will meditate on your precepts.

79May those who fear you turn to me,

those who understand your statutes.

80May I wholeheartedly follow your decrees,

that I may not be put to shame.

כ Kaph

81My soul faints with longing for your salvation,

but I have put my hope in your word.

82My eyes fail, looking for your promise;

I say, “When will you comfort me?”

83Though I am like a wineskin in the smoke,

I do not forget your decrees.

84How long must your servant wait?

When will you punish my persecutors?

85The arrogant dig pits to trap me,

contrary to your law.

86All your commands are trustworthy;

help me, for I am being persecuted without cause.

87They almost wiped me from the earth,

but I have not forsaken your precepts.

88In your unfailing love preserve my life,

that I may obey the statutes of your mouth.

ל Lamedh

89Your word, Lord, is eternal;

it stands firm in the heavens.

90Your faithfulness continues through all generations;

you established the earth, and it endures.

91Your laws endure to this day,

for all things serve you.

92If your law had not been my delight,

I would have perished in my affliction.

93I will never forget your precepts,

for by them you have preserved my life.

94Save me, for I am yours;

I have sought out your precepts.

95The wicked are waiting to destroy me,

but I will ponder your statutes.

96To all perfection I see a limit,

but your commands are boundless.

מ Mem

97Oh, how I love your law!

I meditate on it all day long.

98Your commands are always with me

and make me wiser than my enemies.

99I have more insight than all my teachers,

for I meditate on your statutes.

100I have more understanding than the elders,

for I obey your precepts.

101I have kept my feet from every evil path

so that I might obey your word.

102I have not departed from your laws,

for you yourself have taught me.

103How sweet are your words to my taste,

sweeter than honey to my mouth!

104I gain understanding from your precepts;

therefore I hate every wrong path.

נ Nun

105Your word is a lamp for my feet,

a light on my path.

106I have taken an oath and confirmed it,

that I will follow your righteous laws.

107I have suffered much;

preserve my life, Lord, according to your word.

108Accept, Lord, the willing praise of my mouth,

and teach me your laws.

109Though I constantly take my life in my hands,

I will not forget your law.

110The wicked have set a snare for me,

but I have not strayed from your precepts.

111Your statutes are my heritage forever;

they are the joy of my heart.

112My heart is set on keeping your decrees

to the very end.119:112 Or decrees / for their enduring reward

ס Samekh

113I hate double-minded people,

but I love your law.

114You are my refuge and my shield;

I have put my hope in your word.

115Away from me, you evildoers,

that I may keep the commands of my God!

116Sustain me, my God, according to your promise, and I will live;

do not let my hopes be dashed.

117Uphold me, and I will be delivered;

I will always have regard for your decrees.

118You reject all who stray from your decrees,

for their delusions come to nothing.

119All the wicked of the earth you discard like dross;

therefore I love your statutes.

120My flesh trembles in fear of you;

I stand in awe of your laws.

ע Ayin

121I have done what is righteous and just;

do not leave me to my oppressors.

122Ensure your servant’s well-being;

do not let the arrogant oppress me.

123My eyes fail, looking for your salvation,

looking for your righteous promise.

124Deal with your servant according to your love

and teach me your decrees.

125I am your servant; give me discernment

that I may understand your statutes.

126It is time for you to act, Lord;

your law is being broken.

127Because I love your commands

more than gold, more than pure gold,

128and because I consider all your precepts right,

I hate every wrong path.

פ Pe

129Your statutes are wonderful;

therefore I obey them.

130The unfolding of your words gives light;

it gives understanding to the simple.

131I open my mouth and pant,

longing for your commands.

132Turn to me and have mercy on me,

as you always do to those who love your name.

133Direct my footsteps according to your word;

let no sin rule over me.

134Redeem me from human oppression,

that I may obey your precepts.

135Make your face shine on your servant

and teach me your decrees.

136Streams of tears flow from my eyes,

for your law is not obeyed.

צ Tsadhe

137You are righteous, Lord,

and your laws are right.

138The statutes you have laid down are righteous;

they are fully trustworthy.

139My zeal wears me out,

for my enemies ignore your words.

140Your promises have been thoroughly tested,

and your servant loves them.

141Though I am lowly and despised,

I do not forget your precepts.

142Your righteousness is everlasting

and your law is true.

143Trouble and distress have come upon me,

but your commands give me delight.

144Your statutes are always righteous;

give me understanding that I may live.

ק Qoph

145I call with all my heart; answer me, Lord,

and I will obey your decrees.

146I call out to you; save me

and I will keep your statutes.

147I rise before dawn and cry for help;

I have put my hope in your word.

148My eyes stay open through the watches of the night,

that I may meditate on your promises.

149Hear my voice in accordance with your love;

preserve my life, Lord, according to your laws.

150Those who devise wicked schemes are near,

but they are far from your law.

151Yet you are near, Lord,

and all your commands are true.

152Long ago I learned from your statutes

that you established them to last forever.

ר Resh

153Look on my suffering and deliver me,

for I have not forgotten your law.

154Defend my cause and redeem me;

preserve my life according to your promise.

155Salvation is far from the wicked,

for they do not seek out your decrees.

156Your compassion, Lord, is great;

preserve my life according to your laws.

157Many are the foes who persecute me,

but I have not turned from your statutes.

158I look on the faithless with loathing,

for they do not obey your word.

159See how I love your precepts;

preserve my life, Lord, in accordance with your love.

160All your words are true;

all your righteous laws are eternal.

ש Sin and Shin

161Rulers persecute me without cause,

but my heart trembles at your word.

162I rejoice in your promise

like one who finds great spoil.

163I hate and detest falsehood

but I love your law.

164Seven times a day I praise you

for your righteous laws.

165Great peace have those who love your law,

and nothing can make them stumble.

166I wait for your salvation, Lord,

and I follow your commands.

167I obey your statutes,

for I love them greatly.

168I obey your precepts and your statutes,

for all my ways are known to you.

ת Taw

169May my cry come before you, Lord;

give me understanding according to your word.

170May my supplication come before you;

deliver me according to your promise.

171May my lips overflow with praise,

for you teach me your decrees.

172May my tongue sing of your word,

for all your commands are righteous.

173May your hand be ready to help me,

for I have chosen your precepts.

174I long for your salvation, Lord,

and your law gives me delight.

175Let me live that I may praise you,

and may your laws sustain me.

176I have strayed like a lost sheep.

Seek your servant,

for I have not forgotten your commands.