መዝሙር 118 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 118:1-29

መዝሙር 118

ለዳስ በዓል የቀረበ የጕዞ መዝሙር

1እግዚአብሔር ቸር ነውና አመስግኑት፤

ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

2የእስራኤል ሕዝብ፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።

3የአሮን ቤት፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።

4እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ፣

“ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበሉ።

5በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤

እግዚአብሔርም መለሰልኝ፤ ከመጠበብም አወጣኝ።

6እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው፤ አልፈራም፤ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?

7ይረዳኝ ዘንድ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው፤

የጠላቶቼንም ውድቀት አያለሁ።

8ሰውን መከታ ከማድረግ ይልቅ፣

በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል።

9በገዦች ተስፋ ከማድረግ ይልቅ፣

በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል።

10ሕዝቦች ሁሉ ከበቡኝ፤

ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

11መክበቡንስ በየአቅጣጫው ከበቡኝ፤

ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

12እንደ ንብ መንጋ ከበቡኝ፤

ነገር ግን እንደሚነድድ እሾኽ ከሰሙ፤

በርግጥም በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

13ተገፍትሬ ልወድቅ ተንገደገድሁ፤

እግዚአብሔር ግን ረዳኝ።

14እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

አዳኝ ሆነልኝ።

15በጻድቃን ድንኳን የእልልታና የሆታ ድምፅ፣

እንዲህ እያለ ያስተጋባል፤

የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች፤

16የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለች፤

የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች።”

17ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤

የእግዚአብሔርንም ሥራ ገና እናገራለሁ።

18መገሠጹን እግዚአብሔር እጅግ ገሥጾኛል፤

ነገር ግን ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም።

19የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤

በዚያ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።

20ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤

ጻድቃን በእርሷ በኩል ይገባሉ።

21ሰምተህ መልሰህልኛልና፣

አዳኝም ሆነህልኛልና አመሰግንሃለሁ።

22ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣

እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።

23እግዚአብሔር ይህን አደረገ፤

ለዐይናችንም ድንቅ ናት።

24እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤

በእርሷ ሐሤት እናድርግ፤ ደስም ይበለን።

25እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አድነን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አሳካልን።

26በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው።

ከእግዚአብሔር ቤት ባረክናችሁ።

27እግዚአብሔር አምላክ ነው፤

ብርሃኑንም በላያችን አበራ፤

እስከ መሠዊያው118፥27 ወይም የክብረ በዓልን መሥዋዕት በገመድ ማሰር ወይም መውሰድ ቀንዶች ድረስ በመውጣት፣

ዝንጣፊ ይዛችሁ በዓሉን ከሚያከብሩት ጋር ተቀላቀሉ።

28አንተ አምላኬ ነህ፤ አመሰግንሃለሁ፤

አንተ አምላኬ ነህ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።

29ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

New International Version – UK

Psalms 118:1-29

Psalm 118

1Give thanks to the Lord, for he is good;

his love endures for ever.

2Let Israel say:

‘His love endures for ever.’

3Let the house of Aaron say:

‘His love endures for ever.’

4Let those who fear the Lord say:

‘His love endures for ever.’

5When hard pressed, I cried to the Lord;

he brought me into a spacious place.

6The Lord is with me; I will not be afraid.

What can mere mortals do to me?

7The Lord is with me; he is my helper.

I look in triumph on my enemies.

8It is better to take refuge in the Lord

than to trust in humans.

9It is better to take refuge in the Lord

than to trust in princes.

10All the nations surrounded me,

but in the name of the Lord I cut them down.

11They surrounded me on every side,

but in the name of the Lord I cut them down.

12They swarmed around me like bees,

but they were consumed as quickly as burning thorns;

in the name of the Lord I cut them down.

13I was pushed back and about to fall,

but the Lord helped me.

14The Lord is my strength and my defence118:14 Or song;

he has become my salvation.

15Shouts of joy and victory

resound in the tents of the righteous:

‘The Lord’s right hand has done mighty things!

16The Lord’s right hand is lifted high;

the Lord’s right hand has done mighty things!’

17I will not die but live,

and will proclaim what the Lord has done.

18The Lord has chastened me severely,

but he has not given me over to death.

19Open for me the gates of the righteous;

I will enter and give thanks to the Lord.

20This is the gate of the Lord

through which the righteous may enter.

21I will give you thanks, for you answered me;

you have become my salvation.

22The stone the builders rejected

has become the cornerstone;

23the Lord has done this,

and it is marvellous in our eyes.

24The Lord has done it this very day;

let us rejoice today and be glad.

25Lord, save us!

Lord, grant us success!

26Blessed is he who comes in the name of the Lord.

From the house of the Lord we bless you.118:26 The Hebrew is plural.

27The Lord is God,

and he has made his light shine on us.

With boughs in hand, join in the festal procession

up118:27 Or Bind the festal sacrifice with ropes / and take it to the horns of the altar.

28You are my God, and I will praise you;

you are my God, and I will exalt you.

29Give thanks to the Lord, for he is good;

his love endures for ever.