መዝሙር 118 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 118:1-29

መዝሙር 118

ለዳስ በዓል የቀረበ የጕዞ መዝሙር

1እግዚአብሔር ቸር ነውና አመስግኑት፤

ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

2የእስራኤል ሕዝብ፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።

3የአሮን ቤት፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።

4እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ፣

“ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበሉ።

5በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤

እግዚአብሔርም መለሰልኝ፤ ከመጠበብም አወጣኝ።

6እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው፤ አልፈራም፤ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?

7ይረዳኝ ዘንድ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው፤

የጠላቶቼንም ውድቀት አያለሁ።

8ሰውን መከታ ከማድረግ ይልቅ፣

በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል።

9በገዦች ተስፋ ከማድረግ ይልቅ፣

በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል።

10ሕዝቦች ሁሉ ከበቡኝ፤

ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

11መክበቡንስ በየአቅጣጫው ከበቡኝ፤

ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

12እንደ ንብ መንጋ ከበቡኝ፤

ነገር ግን እንደሚነድድ እሾኽ ከሰሙ፤

በርግጥም በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።

13ተገፍትሬ ልወድቅ ተንገደገድሁ፤

እግዚአብሔር ግን ረዳኝ።

14እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

አዳኝ ሆነልኝ።

15በጻድቃን ድንኳን የእልልታና የሆታ ድምፅ፣

እንዲህ እያለ ያስተጋባል፤

የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች፤

16የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለች፤

የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች።”

17ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤

የእግዚአብሔርንም ሥራ ገና እናገራለሁ።

18መገሠጹን እግዚአብሔር እጅግ ገሥጾኛል፤

ነገር ግን ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም።

19የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤

በዚያ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።

20ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤

ጻድቃን በእርሷ በኩል ይገባሉ።

21ሰምተህ መልሰህልኛልና፣

አዳኝም ሆነህልኛልና አመሰግንሃለሁ።

22ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣

እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።

23እግዚአብሔር ይህን አደረገ፤

ለዐይናችንም ድንቅ ናት።

24እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤

በእርሷ ሐሤት እናድርግ፤ ደስም ይበለን።

25እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አድነን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አሳካልን።

26በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው።

ከእግዚአብሔር ቤት ባረክናችሁ።

27እግዚአብሔር አምላክ ነው፤

ብርሃኑንም በላያችን አበራ፤

እስከ መሠዊያው118፥27 ወይም የክብረ በዓልን መሥዋዕት በገመድ ማሰር ወይም መውሰድ ቀንዶች ድረስ በመውጣት፣

ዝንጣፊ ይዛችሁ በዓሉን ከሚያከብሩት ጋር ተቀላቀሉ።

28አንተ አምላኬ ነህ፤ አመሰግንሃለሁ፤

አንተ አምላኬ ነህ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።

29ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

King James Version

Psalms 118:1-29

1O give thanks unto the LORD; for he is good: because his mercy endureth for ever.

2Let Israel now say, that his mercy endureth for ever.

3Let the house of Aaron now say, that his mercy endureth for ever.

4Let them now that fear the LORD say, that his mercy endureth for ever.

5I called upon the LORD in distress: the LORD answered me, and set me in a large place.118.5 in distress: Heb. out of distress

6The LORD is on my side; I will not fear: what can man do unto me?118.6 on…: Heb. for me

7The LORD taketh my part with them that help me: therefore shall I see my desire upon them that hate me.

8It is better to trust in the LORD than to put confidence in man.

9It is better to trust in the LORD than to put confidence in princes.

10All nations compassed me about: but in the name of the LORD will I destroy them.118.10 destroy…: Heb. cut them off

11They compassed me about; yea, they compassed me about: but in the name of the LORD I will destroy them.

12They compassed me about like bees; they are quenched as the fire of thorns: for in the name of the LORD I will destroy them.118.12 destroy: Heb. cut down

13Thou hast thrust sore at me that I might fall: but the LORD helped me.

14The LORD is my strength and song, and is become my salvation.

15The voice of rejoicing and salvation is in the tabernacles of the righteous: the right hand of the LORD doeth valiantly.

16The right hand of the LORD is exalted: the right hand of the LORD doeth valiantly.

17I shall not die, but live, and declare the works of the LORD.

18The LORD hath chastened me sore: but he hath not given me over unto death.

19Open to me the gates of righteousness: I will go into them, and I will praise the LORD:

20This gate of the LORD, into which the righteous shall enter.

21I will praise thee: for thou hast heard me, and art become my salvation.

22The stone which the builders refused is become the head stone of the corner.

23This is the LORD’s doing; it is marvellous in our eyes.118.23 the LORD’s…: Heb. from the LORD

24This is the day which the LORD hath made; we will rejoice and be glad in it.

25Save now, I beseech thee, O LORD: O LORD, I beseech thee, send now prosperity.

26Blessed be he that cometh in the name of the LORD: we have blessed you out of the house of the LORD.

27God is the LORD, which hath shewed us light: bind the sacrifice with cords, even unto the horns of the altar.

28Thou art my God, and I will praise thee: thou art my God, I will exalt thee.

29O give thanks unto the LORD; for he is good: for his mercy endureth for ever.