መዝሙር 116 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 116:1-19

መዝሙር 116

ምስጋና

1የልመናዬን ድምፅ ሰምቷልና፣

እግዚአብሔርን ወደድሁት።

2ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሏልና፣

በሕይወት ዘመኔ ሁሉ ወደ እርሱ እጣራለሁ።

3የሞት ወጥመድ ያዘኝ፤

የሲኦልም116፥3 ዕብራይስጡ መቃብር ይላል። ጣር አገኘኝ፤

ጭንቅና ሐዘን አሸነፈኝ።

4እኔም የእግዚአብሔርን ስም ጠራሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ነፍሴን ታድናት ዘንድ እለምንሃለሁ” አልሁ።

5እግዚአብሔር ቸርና ጻድቅ ነው፤

አምላካችን መሓሪ ነው።

6እግዚአብሔር ገሮችን ይጠብቃል፤

እጅግ ተቸግሬ ሳለሁ አዳነኝ።

7ነፍሴ ሆይ፤ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፤

እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤

8አንተ ነፍሴን ከሞት፣

ዐይኔን ከእንባ፣

እግሮቼን ከመሰናከል አድነሃልና።

9እኔም በሕያዋን ምድር፣

በእግዚአብሔር ፊት እመላለሳለሁ።

10“እጅግ ተጨንቄአለሁ” ባልሁበት ጊዜ እንኳ፣116፥10 ወይም ያኔ እንኳን

እምነቴን ጠብቄአለሁ።

11ግራ በተጋባሁ ጊዜ፣

“ሰው ሁሉ ሐሰተኛ ነው” አልሁ።

12ስለ ዋለልኝ ውለታ ሁሉ፣

ለእግዚአብሔር ምን ልክፈለው?

13የመዳንን ጽዋ አነሣለሁ፤

የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ።

14በሕዝቡ ሁሉ ፊት፣

ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ።

15የቅዱሳኑ ሞት፣

በእግዚአብሔር ፊት የተከበረ ነው።

16እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔ በእውነት ባሪያህ ነኝ፤

እኔ የሴት ባሪያህ116፥16 ታማኝ አገልጋይህ ወይም ታማኝ ልጅህ ልጅ፣ ባሪያህ ነኝ፤

ከእስራቴም ፈታኸኝ።

17ለአንተ የምስጋና መሥዋዕት አቀርባለሁ፤

የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ።

18በሕዝቡ ሁሉ ፊት፣

ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ፤

19ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ይህን በመካከልሽ፣

በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ አደርጋለሁ።

ሃሌ ሉያ።116፥19 አንዳንዶች እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

New International Version

Psalms 116:1-19

Psalm 116

1I love the Lord, for he heard my voice;

he heard my cry for mercy.

2Because he turned his ear to me,

I will call on him as long as I live.

3The cords of death entangled me,

the anguish of the grave came over me;

I was overcome by distress and sorrow.

4Then I called on the name of the Lord:

Lord, save me!”

5The Lord is gracious and righteous;

our God is full of compassion.

6The Lord protects the unwary;

when I was brought low, he saved me.

7Return to your rest, my soul,

for the Lord has been good to you.

8For you, Lord, have delivered me from death,

my eyes from tears,

my feet from stumbling,

9that I may walk before the Lord

in the land of the living.

10I trusted in the Lord when I said,

“I am greatly afflicted”;

11in my alarm I said,

“Everyone is a liar.”

12What shall I return to the Lord

for all his goodness to me?

13I will lift up the cup of salvation

and call on the name of the Lord.

14I will fulfill my vows to the Lord

in the presence of all his people.

15Precious in the sight of the Lord

is the death of his faithful servants.

16Truly I am your servant, Lord;

I serve you just as my mother did;

you have freed me from my chains.

17I will sacrifice a thank offering to you

and call on the name of the Lord.

18I will fulfill my vows to the Lord

in the presence of all his people,

19in the courts of the house of the Lord

in your midst, Jerusalem.

Praise the Lord.116:19 Hebrew Hallelu Yah