መዝሙር 115 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 115:1-18

መዝሙር 115

አንዱ እውነተኛው አምላክ

115፥4-11 ተጓ ምብ – መዝ 135፥15-20

1ለእኛ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለእኛ ሳይሆን፣

ስለ ምሕረትህና ስለ እውነትህ፣

ለስምህ ክብርን ስጥ።

2አሕዛብ፣ “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ?

3አምላካችንስ በሰማይ ነው፤

እርሱ ደስ የሚለውን ያደርጋል።

4የእነርሱ ጣዖታት ግን የሰው እጅ የሠራቸው፣

ብርና ወርቅ ናቸው።

5አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፣

6ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

አፍንጫ አላቸው፤ አያሸትቱም፤

7እጅ አላቸው፤ አይዳስሱም፤

እግር አላቸው፤ አይሄዱም፤

በጕሮሯቸውም ድምፅ አይፈጥሩም።

8እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

9የእስራኤል ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

10የአሮን ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

11እናንተ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

12እግዚአብሔር ያስበናል፤ ይባርከናልም፤

እርሱ የእስራኤልን ቤት ይባርካል፤

የአሮንንም ቤት ይባርካል።

13እግዚአብሔርን የሚፈሩትን ሁሉ፣

ትልቁንም ትንሹንም ይባርካል።

14እግዚአብሔር እናንተንና ልጆቻችሁን፣

በባርኮቱ ያብዛችሁ።

15ሰማይንና ምድርን በፈጠረ፣

በእግዚአብሔር የተባረካችሁ ሁኑ።

16ሰማየ ሰማያት የእግዚአብሔር ናቸው፤

ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።

17እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑት የሞቱት አይደሉም፤

ወደ ዝምታው ዓለም የሚወርዱም አይደሉም።

18ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣

እግዚአብሔርን የምንባርክ እኛ ነን።

እግዚአብሔር ይመስገን።115፥18 ዕብራይስጡ ሃሌ ሉያ ይላል።

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 115:1-18

Psalm 115

Herren tillhör all ära

1Inte åt oss, Herre, inte åt oss,

utan åt ditt namn ge ära,

för din nåds och din trofasthets skull.

2Varför får folk säga:

”Var finns deras Gud?”

3Vår Gud är i himlen,

och han gör vad han vill.

4Deras gudar är silver och guld,

människohänders verk.

5De har mun men kan inte tala,

ögon, men kan inte se.

6De har öron men kan inte höra,

näsa, men kan inte lukta.

7De har händer, men kan inte gripa,

och fötter, men kan inte gå.

De ger inga ljud ifrån sin strupe.

8De som gjort dessa blir som de,

ja, alla som förtröstar på dem.

9Israel, förtrösta på Herren!

Han är deras hjälp och sköld.

10Arons släkt, förtrösta på Herren!

Han är deras hjälp och sköld.

11Alla ni som fruktar Herren, förtrösta på honom!

Han är deras hjälp och sköld.

12Herren tänker på oss

och vill välsigna Israels folk,

han vill välsigna Arons släkt.

13Han vill välsigna var och en som fruktar Herren,

små och stora.

14Herren ge många barn till er och era ättlingar.

15Må ni bli välsignade av Herren,

som har gjort både himmel och jord.

16Himlen tillhör Herren,

men han har överlämnat jorden åt människorna.

17De döda prisar inte Herren,

de som har gått ner i tystnaden.

18Men vi lovar Herren, nu och för evigt!

Halleluja!