መዝሙር 113 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 113:1-9

መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በ9 ላይም ይገኛል።

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርን ስም አወድሱ።

2ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

3ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

4እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

Persian Contemporary Bible

مزامير 113:1-9

در ستايش نيكويی خداوند

1خداوند را سپاس باد!

ای بندگان خداوند، نام او را ستايش كنيد! 2نام او از حال تا ابد ستوده شود. 3از طلوع آفتاب تا غروب آن، نام خداوند را ستايش كنيد! 4خداوند بر همهٔ قومها حكمرانی می‌كند؛ شكوه او برتر از آسمانهاست.

5خداوند، خدای ما كه در آسمانها نشسته است، همتا و مانندی ندارد.

6‏-8او از آسمان بر زمين نظر می‌افكند تا شخص فروتن و فقير را از خاک بلند كند و سرافراز نمايد و او را در رديف بزرگان قوم خويش قرار دهد. 9خداوند با بخشيدن فرزندان به زن نازا او را خوشحال و سرافراز می‌سازد.

خداوند را سپاس باد!