መዝሙር 113 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 113:1-9

መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በ9 ላይም ይገኛል።

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርን ስም አወድሱ።

2ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

3ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

4እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

King James Version

Psalms 113:1-9

1Praise ye the LORD. Praise, O ye servants of the LORD, praise the name of the LORD.113.1 Praise ye…: Heb. Hallelujah

2Blessed be the name of the LORD from this time forth and for evermore.

3From the rising of the sun unto the going down of the same the LORD’s name is to be praised.

4The LORD is high above all nations, and his glory above the heavens.

5Who is like unto the LORD our God, who dwelleth on high,113.5 dwelleth…: Heb. exalteth himself to dwell

6Who humbleth himself to behold the things that are in heaven, and in the earth!

7He raiseth up the poor out of the dust, and lifteth the needy out of the dunghill;

8That he may set him with princes, even with the princes of his people.

9He maketh the barren woman to keep house, and to be a joyful mother of children. Praise ye the LORD.113.9 to keep…: Heb. to dwell in an house