መዝሙር 113 – NASV & CST

New Amharic Standard Version

መዝሙር 113:1-9

መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በ9 ላይም ይገኛል።

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርን ስም አወድሱ።

2ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

3ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

4እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

Nueva Versión Internacional (Castilian)

Salmo 113:1-9

Salmo 113

1¡Aleluya! ¡Alabado sea el Señor!

Alabad, siervos del Señor,

alabad el nombre del Señor.

2Bendito sea el nombre del Señor,

desde ahora y para siempre.

3Desde la salida del sol hasta su ocaso,

sea alabado el nombre del Señor.

4El Señor domina sobre todas las naciones;

su gloria está sobre los cielos.

5¿Quién como el Señor nuestro Dios,

que tiene su trono en las alturas

6y se digna contemplar los cielos y la tierra?

7Él levanta del polvo al pobre

y saca del muladar al necesitado;

8los hace sentarse con príncipes,

con los príncipes de su pueblo.

9A la mujer estéril le da un hogar

y le concede la dicha de ser madre.

¡Aleluya! ¡Alabado sea el Señor!