መዝሙር 113 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 113:1-9

መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በ9 ላይም ይገኛል።

የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርን ስም አወድሱ።

2ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

3ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

4እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 113:1-9

第 113 篇

讚美上帝的美善

1你們要讚美耶和華!

耶和華的僕人啊,

你們要讚美,讚美耶和華。

2願耶和華的名受稱頌,

從現在直到永遠!

3從日出之地到日落之處,

普世都應當讚美耶和華。

4耶和華高居萬國之上,

祂的榮耀高過諸天。

5誰能與我們的上帝耶和華相比?

祂坐在至高之處,

6俯視諸天和大地。

7祂從灰塵中提拔貧窮人,

從糞堆中擢升困苦人,

8使他們與王子同坐,

與本國的王子同坐。

9祂賜給不育的婦人兒女,

使她們成為快樂的母親。

你們要讚美耶和華!