መዝሙር 112 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 112:1-10

መዝሙር 112

የጻድቅ ሰው ባሕርይ

1ሃሌ ሉያ።112፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ነው።

እግዚአብሔርን የሚፈራ፣

በትእዛዙም እጅግ ደስ የሚሰኝ የተባረከ ነው።

2ዘሩ በምድር ላይ ኀያል ይሆናል፤

የቅኖች ትውልድ ትባረካለች።

3ሀብትና ብልጽግና በቤቱ ይሞላል፤

ጽድቁም ለዘላለም ይኖራል።

4ቸር፣ ርኅሩኅና ጻድቅ እንደ መሆኑ፣

ለቅን ሰው በጨለማ ውስጥ ብርሃን ይወጣለታል።

5ለጋስና ያለ ማንገራገር የሚያበድር፣

ሥራውንም በትክክል የሚያከናውን ሰው መልካም ይሆንለታል፤

6ለዘላለም ከስፍራው አይናወጥምና፤

ጻድቅ ሰው ሲታወስ ይኖራል።

7ክፉ ወሬ አያሸብረውም፤

ልቡ እግዚአብሔርን በመተማመን የጸና ነው።

8ልቡ የጸና ነው፤ አይፈራምም፤

በመጨረሻም የጠላቶቹን ውድቀት ያያል።

9በልግስና ለድኾች ሰጠ፤

ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል፤

ቀንዱም112፥9 በዚህ ስፍራ ክብርን ያመለክታል። በክብር ከፍ ከፍ ይላል።

10ክፉ ሰው ይህን በማየት ይበሳጫል፤

ጥርሱን ያፋጫል፤ እየመነመነም ይጠፋል፤

የክፉዎችም ምኞት ትጠፋለች።

King James Version

Psalms 112:1-10

1Praise ye the LORD. Blessed is the man that feareth the LORD, that delighteth greatly in his commandments.112.1 Praise…: Heb. Hallelujah

2His seed shall be mighty upon earth: the generation of the upright shall be blessed.

3Wealth and riches shall be in his house: and his righteousness endureth for ever.

4Unto the upright there ariseth light in the darkness: he is gracious, and full of compassion, and righteous.

5A good man sheweth favour, and lendeth: he will guide his affairs with discretion.112.5 discretion: Heb. judgment

6Surely he shall not be moved for ever: the righteous shall be in everlasting remembrance.

7He shall not be afraid of evil tidings: his heart is fixed, trusting in the LORD.

8His heart is established, he shall not be afraid, until he see his desire upon his enemies.

9He hath dispersed, he hath given to the poor; his righteousness endureth for ever; his horn shall be exalted with honour.

10The wicked shall see it, and be grieved; he shall gnash with his teeth, and melt away: the desire of the wicked shall perish.