መዝሙር 111 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 111:1-10

መዝሙር 111111 የግጥሙ መሥመሮች እያንዳንዳቸው ከላይ እስከ ታች በተከታታይ በዕብራይስጥ ፊደሎች ቅደም ተከተል የተቀመጡ ናቸው።

ለመለኮቱ ባሕርያት የቀረበ ጸሎት

1ሃሌ ሉያ።

በቅኖች ሸንጎ፣ በጉባኤም መካከል፣

ለእግዚአብሔር በፍጹም ልቤ ምስጋና አቀርባለሁ።

2የእግዚአብሔር ሥራ ታላቅ ናት፤

ደስ የሚሰኙባትም ሁሉ ያውጠነጥኗታል።

3ሥራው ባለ ክብርና ባለ ግርማ ነው፤

ጽድቁም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

4ድንቅ ሥራው ሲታወስ እንዲኖር አደረገ፤

እግዚአብሔር ቸር፣ ርኅሩኅም ነው።

5ለሚፈሩት ምግብን ይሰጣል፤

ኪዳኑንም ለዘላለም ያስባል።

6ለሕዝቡ የአሕዛብን ርስት በመስጠት፣

የአሠራሩን ብርታት አሳይቷል።

7የእጁ ሥራ እውነተኛና ቅን ነው፤

ሥርዐቱም ሁሉ የታመነ ነው፤

8ከዘላለም እስከ ለዘላለም የጸና ነው፤

በእውነትና በቅንነትም የተሠራ ነው።

9ለሕዝቡ መዳንን ሰደደ፤

ኪዳኑንም ለዘላለም አዘዘ፤

ስሙም የተቀደሰና የተፈራ ነው።

10እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ መጀመሪያ ነው፤

ትእዛዙንም የሚፈጽሙ ጥሩ ማስተዋል አላቸው፤

ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 111:1-10

111

1-2ハレルヤ。

私がどれほど主に感謝しているか、

人々に知ってほしいと思います。

感謝を忘れない人たちよ、

さあいっしょに、主のなさった数々の奇跡を

思い巡らしましょう。

3この奇跡こそ、神の栄誉と威厳、

そして永遠の恵みを物語るものです。

4だれが、主のあわれみと恵みを簡単に忘れるでしょう。

5主はご自分に信頼を寄せる人に食物を与え、

決して約束を破棄なさいません。

6神はご自分の民を大きな力で支え、

多くの民族が住んでいた、

イスラエルの地をお与えになりました。

7神のなさることはみな正しく、

そのおきてはどれ一つ取っても誤りがありません。

8神のおきては真理と恵みで成り立っていて、

永遠に続きます。

9主に身の代金を払っていただいた民は、

今や自由に神の前に出入りできるのです。

10人はどうすれば知恵をみがけるでしょうか。

それには、主を信じて従うことです。

神のおきてを守ってこそ、賢くなれるのです。

神を永遠にほめたたえましょう。