መዝሙር 110 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 110:1-7

መዝሙር 110

መሲሑ ንጉሥና ካህን

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ጌታዬን፣

“ጠላቶችህን ለእግርህ መርገጫ፣

እስከማደርግልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ” አለው።

2እግዚአብሔር ብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰድዳል፤

አንተም በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።

3ለጦርነት በምትወጣበት ቀን፣

ሰራዊትህ በገዛ ፈቃዱ በጐንህ ይቆማል፤

ከንጋት ማሕፀን፣

በቅዱስ ግርማ ደምቀህ፣

የጕልማሳነትህን ልምላሜ110፥3 ወይም ጐልማሶችህ እንደ ንጋት ወዳንተ ይመጣሉ ማለት ነው። እንደ ጠል ትቀበላለህ።

4“እንደ መልከጼዴቅ ሥርዐት፤

አንተ ለዘላለም ካህን ነህ” ብሎ፣

እግዚአብሔር ምሏል፤

እርሱ ሐሳቡን አይለውጥም።

5ጌታ በቀኝህ ነው፤

በቍጣውም ቀን ነገሥታትን ያደቅቃቸዋል።

6በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤

በየአገሩ ያሉትንም ራሶች ከስክሶ ሬሳ በሬሳ ያደርጋቸዋል።

7መንገድ110፥7 ወይም ሥልጣን ለመስጠት ኀይል ያለው ሥልጣን ላይ ያስቀምጠዋል ዳር ካለች ፈሳሽ ውሃ ይጠጣል፤

ስለዚህ ራሱን ቀና ያደርጋል።

Het Boek

Psalmen 110:1-7

1Een psalm van David.

Dit sprak de Here tot mijn Heer:

‘Kom naast Mij zitten, aan mijn rechterhand,

totdat Ik uw vijanden aan u onderworpen heb.’

2De Here laat u machtig heersen vanuit Sion.

U bent de overwinnaar over al uw tegenstanders.

3Uw volk volgt u graag

als u het oproept voor de strijd.

Al heel vroeg in de morgen verschijnen

de sterke jongemannen in prachtige kleding.

4De Here heeft een eed afgelegd

waarvan Hij nimmer spijt krijgt:

‘U bent de eeuwige priester,

zoals ook Melchisedek mijn priester was.’

5De Here is aan uw rechterzijde

en verlaat u niet.

Op de dag van zijn toorn

vernietigt Hij de koningen van deze aarde.

6Hij spreekt het vonnis over de ongelovigen uit

en de lijken stapelen zich op.

Hij vernietigt hen, waar zij ook zijn.

7Onderweg lest Hij zijn dorst bij een beek

en Hij draagt het hoofd fier opgeheven.