መዝሙር 108 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 108:1-13

መዝሙር 108

የጧት ውዳሴና ብሔራዊ ጸሎት

108፥1-5 ተጓ ምብ – መዝ 57፥7-11

108፥6-13 ተጓ ምብ – መዝ 60፥5-12

የዳዊት መዝሙር፤ ማሕሌት።

1አምላክ ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤

እዘምራለሁ፤ በፍጹም ነፍሴም እዘምራለሁ።

2በገናም መሰንቆም ተነሡ፤

እኔም ማልጄ እነሣለሁ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ በሕዝብ መካከል አመሰግንሃለሁ፤

በሕዝቦችም መካከል እዘምርልሃለሁ።

4ምሕረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናትና፤

ታማኝነትህም እስከ ጠፈር ትደርሳለች።

5አምላክ ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትንሰራፋ።

6ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣

በቀኝ እጅህ ታደግ፤ መልስልኝም።

7እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ አለ፤

ደስ እያለኝ ሴኬምን እሸነሽናለሁ፤

“የሱኮትንም ሸለቆ እለካለሁ።

8ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤

ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤

ይሁዳም በትረ መንግሥቴ።

9ሞዓብ መታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤

በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤

በፍልስጥኤም ላይ በድል አድራጊነት እፎክራለሁ።”

10ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ይወስደኛል?

ወደ ኤዶምያስስ ማን ያደርሰኛል?

11እግዚአብሔር ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?

አምላክ ሆይ፤ ከሰራዊታችንም ጋር አልወጣ አልህ!

12አሁንም የሰው ማዳን ከንቱ ነውና፣

በጠላታችን ላይ ድልን አቀዳጀን።

13እግዚአብሔር ሲረዳን ብርቱ እንሆናለን፤

ጠላቶቻችንንም ከእግሩ በታች የሚረግጥ እርሱ ነው።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 108:1-13

สดุดี 108

(สดด.57:7-11; 60:5-12)

(บทเพลง บทสดุดีของดาวิด)

1ข้าแต่พระเจ้า จิตใจของข้าพระองค์แน่วแน่

ข้าพระองค์จะขับร้องและบรรเลงดนตรีด้วยสุดจิตสุดใจ

2พิณใหญ่และพิณเขาคู่ จงบรรเลงเถิด!

ข้าพเจ้าจะปลุกรุ่งอรุณ

3ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ข้าพระองค์จะสรรเสริญพระองค์ในหมู่ประชาชาติ

ข้าพระองค์จะร้องเพลงสรรเสริญพระองค์ท่ามกลางชนชาติต่างๆ

4เพราะความรักมั่นคงของพระองค์ยิ่งใหญ่สูงส่งเหนือฟ้าสวรรค์

ความซื่อสัตย์ของพระองค์ถึงท้องฟ้า

5ข้าแต่พระเจ้า ขอทรงเป็นที่ยกย่องเทิดทูนเหนือฟ้าสวรรค์

ขอพระเกียรติสิริของพระองค์ครอบคลุมไปทั่วโลก

6ขอทรงช่วยกู้ข้าพระองค์ทั้งหลายด้วยพระหัตถ์ขวาของพระองค์

เพื่อบรรดาผู้ที่พระองค์ทรงรักจะรอดพ้น

7พระเจ้าตรัสจากสถานนมัสการของพระองค์ว่า

“ในชัยชนะ เราจะแบ่งเชเคม

และกำหนดเขตหุบเขาสุคคท

8กิเลอาดเป็นของเรา มนัสเสห์เป็นของเรา

เอฟราอิมคือหมวกเกราะของเรา

ยูดาห์คือคทาของเรา

9โมอับเป็นอ่างชำระของเรา

เราเหวี่ยงรองเท้าของเราลงบนเอโดม

และเราจะโห่ร้องด้วยความมีชัยเหนือฟีลิสเตีย”

10ใครจะพาข้าพระองค์ไปยังเมืองป้อมปราการ?

ใครจะนำข้าพระองค์ไปยังเอโดม?

11พระองค์ไม่ใช่หรือ ข้าแต่พระเจ้า พระองค์ผู้ได้ทรงทอดทิ้งข้าพระองค์ทั้งหลาย

และไม่ทรงร่วมทัพกับเหล่าข้าพระองค์อีกต่อไป?

12ขอทรงช่วยข้าพระองค์ทั้งหลายต่อสู้ข้าศึก

เพราะความช่วยเหลือของมนุษย์นั้นไร้ค่า

13โดยพระเจ้าเราจะมีชัยชนะ

พระองค์จะทรงเหยียบย่ำศัตรูของเรา