መዝሙር 108 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 108:1-13

መዝሙር 108

የጧት ውዳሴና ብሔራዊ ጸሎት

108፥1-5 ተጓ ምብ – መዝ 57፥7-11

108፥6-13 ተጓ ምብ – መዝ 60፥5-12

የዳዊት መዝሙር፤ ማሕሌት።

1አምላክ ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤

እዘምራለሁ፤ በፍጹም ነፍሴም እዘምራለሁ።

2በገናም መሰንቆም ተነሡ፤

እኔም ማልጄ እነሣለሁ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ በሕዝብ መካከል አመሰግንሃለሁ፤

በሕዝቦችም መካከል እዘምርልሃለሁ።

4ምሕረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናትና፤

ታማኝነትህም እስከ ጠፈር ትደርሳለች።

5አምላክ ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትንሰራፋ።

6ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣

በቀኝ እጅህ ታደግ፤ መልስልኝም።

7እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ አለ፤

ደስ እያለኝ ሴኬምን እሸነሽናለሁ፤

“የሱኮትንም ሸለቆ እለካለሁ።

8ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤

ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤

ይሁዳም በትረ መንግሥቴ።

9ሞዓብ መታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤

በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤

በፍልስጥኤም ላይ በድል አድራጊነት እፎክራለሁ።”

10ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ይወስደኛል?

ወደ ኤዶምያስስ ማን ያደርሰኛል?

11እግዚአብሔር ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?

አምላክ ሆይ፤ ከሰራዊታችንም ጋር አልወጣ አልህ!

12አሁንም የሰው ማዳን ከንቱ ነውና፣

በጠላታችን ላይ ድልን አቀዳጀን።

13እግዚአብሔር ሲረዳን ብርቱ እንሆናለን፤

ጠላቶቻችንንም ከእግሩ በታች የሚረግጥ እርሱ ነው።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 108:1-13

108

1ああ神よ。

賛美が私の口からあふれてきます。

心から喜んで、あなたへの歌をささげましょう。

2十弦の琴と竪琴よ、目覚めなさい。

共々に歌って、夜明けを迎えようではないか。

3私は世界のどこでも、主をたたえます。

4あなたの恵みは測り知れず、

その真実は天にまで達します。

5ご栄光は、大空を突き抜くようにそびえています。

6あなたが愛しておられる子、

私の叫びを聞いてください。

あなたの偉大な力で、私を救ってください。

7神が聖なる約束を交わしてくださったので

私はほめたたえます。

神は、シェケムの全土とスコテの谷を下さると

約束してくださいました。

8「ギルアデとマナセは、

おまえたちに与える、わたしの領地だ。

エフライムは、わたしのかぶと、ユダはわたしの笏。

9しかし、モアブとエドムはさげすまされる。

わたしはペリシテ人に向かって、勝ちどきを上げよう。」

10神以外のだれが、こんな要塞で固められた町々を

征服する力を、私に授けてくれるでしょう。

また、エドムまで導いてくれるでしょう。

11神よ、あなたは私たちを見捨て、

その軍勢を置き去りになさったのでしょうか。

12どうか、敵に立ち向かう力を与えてください。

同盟軍の助けなどあてにできません。

13神の助けさえあれば、

勇敢に戦うことができます。

神が敵を踏みにじってくださるからです。