መዝሙር 107 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 107:1-43

አምስተኛ መጽሐፍ

ከመዝሙር 107–150

መዝሙር 107

ከመከራ ሁሉ የሚታደግ አምላክ

1ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

ምሕረቱም ለዘላለም ነውና።

2እግዚአብሔር የተቤዣቸው፣

ከጠላት እጅ የታደጋቸው ይህን ይበሉ፤

3ከምሥራቅና ከምዕራብ፣ ከሰሜንና ከደቡብ፣107፥3 ዕብራይስጡ ሰሜንና ባሕሩ ይለዋል።

ከየአገሩ የሰበሰባቸው እንዲህ ይናገሩ።

4አንዳንዶቹ ጭው ባለ በረሓ ተቅበዘበዙ፤

ወደሚኖሩባት ከተማ የሚያደርስ መንገድ ዐጡ።

5ተራቡ፤ ተጠሙ፤

ነፍሳቸውም በውስጣቸው ዛለች።

6በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤

እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው።

7ወደሚኖሩባትም ከተማ፣

በቀና መንገድ መራቸው።

8እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ፣

ለሰው ልጆችም ስላደረገው ድንቅ ሥራ ያመስግኑት፤

9እርሱ የተጠማችውን ነፍስ አርክቷልና፤

የተራበችውንም ነፍስ በበጎ ነገር አጥግቧል።

10አንዳንዶቹ በብረት ሰንሰለት ታስረው የተጨነቁ፣

በጨለማ፣ በጥልማሞት ውስጥ የተቀመጡ ነበሩ፤

11በእግዚአብሔር ቃል ላይ በማመፅ፣

የልዑልን ምክር አቃልለዋልና።

12ስለዚህ በጕልበት ሥራ ልባቸውን አዛለ፤

ተዝለፈለፉ፤ የሚደግፋቸውም አልነበረም።

13በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤

እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው።

14ከጨለማና ከጥልማሞት አወጣቸው፤

እስራታቸውንም በጠሰላቸው።

15እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ፣

ለሰው ልጆችም ስላደረገው ድንቅ ሥራ ያመስግኑት፤

16እርሱ የናሱን በሮች ሰብሯልና፤

የብረቱንም መወርወሪያ ቈርጧል።

17አንዳንዶቹ ከዐመፃቸው የተነሣ ቂሎች ሆኑ፤

ከበደላቸው የተነሣ ችግር ውስጥ ገቡ።

18ሰውነታቸው የምግብ ዐይነት ሁሉ ተጸየፈች፤

ወደ ሞትም ደጆች ቀረቡ።

19በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤

እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው።

20ቃሉን ልኮ ፈወሳቸው፤

ከመቃብርም አፋፍ መለሳቸው።

21እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ፣

ለሰው ልጆችም ስላደረገው ድንቅ ሥራ ያመስግኑት፤

22የምስጋናም መሥዋዕት ያቅርቡለት፤

ሥራውንም ደስ በሚል ዝማሬ ይግለጹ።

23አንዳንዶቹ በመርከብ ወደ ባሕር ወረዱ፤

በታላቅም ውሃ ላይ ሥራቸውን አከናወኑ፤

24የእግዚአብሔርን ሥራ በዚያ አዩ፤

ድንቅ አድራጎቱንም በጥልቁ ውስጥ ተመለከቱ።

25እርሱ ተናግሮ ዐውሎ ነፋስን አስነሣ፤

ነፋሱም ማዕበሉን ከፍ ከፍ አደረገ።

26ወደ ሰማይ ወጡ፤ ወደ ጥልቅም ወረዱ፤

ከመከራቸውም የተነሣ ሐሞታቸው ፈሰሰ።

27እንደ ሰከረ ሰው ዞሮባቸው ወዲያ ወዲህ ተንገዳገዱ፤

መላው ጠፍቶባቸው የሚያደርጉትን ዐጡ።

28በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤

እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው።

29ዐውሎ ነፋሱን ጸጥ አደረገ፤

የባሕሩም ሞገድ ረጭ አለ።

30ጸጥ በማለቱም ደስ አላቸው፤

ወዳሰቡትም ወደብ አደረሳቸው።

31እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ፣

ለሰው ልጆችም ስላደረገው ድንቅ ሥራ ያመስግኑት፤

32በሕዝብ ጉባኤ መካከል ከፍ ከፍ ያድርጉት፤

በሽማግሌዎችም ሸንጎ ይወድሱት።

33ወንዞችን ወደ ምድረ በዳ፣

የውሃ ምንጮችንም ወደ ደረቅ ምድር ለወጠ።

34ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሣ፣

ፍሬያማዋን ምድር በጨው የተበከለች አደረጋት።

35ምድረ በዳውን ወደ ውሃ መከማቻ፣

ደረቁንም ምድር ወደ ውሃ ምንጭ ቀየረ።

36የተራቡትን በዚያ አስቀመጠ፤

የሚኖሩባትንም ከተማ ሠሩ።

37በዕርሻውም ዘሩበት፤ ወይንም ተከሉ፤

ብዙ ፍሬም አመረቱ።

38ይባርካቸዋል፤ እነርሱም እጅግ ይበዛሉ፤

የከብቶቻቸውም ብዛት እንዲያንስ አያደርግም።

39በጭንቅ፣ በመከራና በሐዘን፣

ቍጥራቸው አንሶ፣ ተዋርደው ነበር፤

40በመኳንንቱም ላይ መናቅን አዘነበባቸው፤

መውጫ መግቢያው በማይታወቅ በረሓ ውስጥም አንከራተታቸው።

41ችግረኞችን ግን ከጭንቀታቸው መዝዞ አወጣቸው፤

ቤተ ሰባቸውንም እንደ በግ መንጋ አበዛ።

42ልበ ቅኖች ይህን አይተው ሐሤት ያደርጋሉ፤

ጥመትም ሁሉ አፏን ትዘጋለች።

43እንግዲህ ማንም ብልኅ ቢሆን፣ ይህን ነገር ልብ ይበል፤

እርሱም የእግዚአብሔርን ምሕረት ያስተውላል።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 107:1-43

บรรพ 5

สดุดี 107—150

สดุดี 107

1จงขอบพระคุณองค์พระผู้เป็นเจ้าเพราะพระองค์ทรงแสนดี

ความรักมั่นคงของพระองค์ดำรงนิรันดร์

2ให้ผู้ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงไถ่กล่าวเช่นนี้

คือผู้ที่ทรงไถ่จากเงื้อมมือของศัตรู

3ผู้ที่พระองค์ทรงรวบรวมมาจากดินแดนต่างๆ

จากตะวันออกและตะวันตก จากเหนือและใต้107:3 ภาษาฮีบรูว่าเหนือและทะเล

4บางคนระเหเร่ร่อนอยู่ในถิ่นกันดารแห้งแล้ง

ไม่พบทางไปเมืองที่พวกเขาจะตั้งถิ่นฐาน

5พวกเขาทั้งหิวและกระหาย

อ่อนแรงใจจะขาด

6แล้วพวกเขาร้องทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าในความทุกข์ยาก

พระองค์ก็ทรงปลดปล่อยพวกเขาจากความทุกข์เข็ญ

7พระองค์ทรงนำพวกเขาไปในทางตรง

ไปเมืองที่พวกเขาจะตั้งถิ่นฐานได้

8ให้พวกเขาขอบพระคุณองค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับความรักมั่นคงของพระองค์

และสำหรับพระราชกิจมหัศจรรย์ของพระองค์ที่ทำเพื่อมนุษย์

9เพราะว่าพระองค์ทรงให้คนที่กระหายได้อิ่มเอม

ทรงให้ผู้ที่หิวโหยอิ่มด้วยสิ่งดี

10บางคนนั่งอยู่ในความมืดมิดหม่นหมอง

ถูกจองจำทุกข์ทรมานด้วยโซ่ตรวน

11เพราะพวกเขากบฏต่อพระวจนะของพระเจ้า

และดูหมิ่นคำแนะนำสั่งสอนขององค์ผู้สูงสุด

12ฉะนั้นพระองค์ทรงสยบพวกเขาด้วยงานหนัก

พวกเขาล้มลงและไม่มีใครช่วย

13แล้วพวกเขาร้องทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าในความทุกข์ยาก

และพระองค์ทรงช่วยพวกเขาให้รอดจากความทุกข์เข็ญ

14พระองค์ทรงนำพวกเขาออกมาจากความมืดมิดหม่นหมอง

และทรงทำลายโซ่ตรวนของพวกเขา

15ให้พวกเขาขอบพระคุณองค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับความรักมั่นคงของพระองค์

และสำหรับพระราชกิจมหัศจรรย์ของพระองค์ที่ทำเพื่อมนุษย์

16เพราะพระองค์ทรงทลายประตูทองสัมฤทธิ์

และตัดลูกกรงเหล็กออก

17บางคนกลายเป็นคนโง่โดยการกบฏของตัวเอง

และต้องทนทุกข์เพราะความชั่วช้าของตน

18พวกเขาเบื่ออาหารทุกอย่าง

และเฉียดใกล้ประตูแห่งความตาย

19แล้วพวกเขาร้องทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าในความทุกข์ยาก

และพระองค์ทรงช่วยพวกเขาให้รอดจากความทุกข์เข็ญ

20พระองค์ตรัส พวกเขาก็ได้รับการรักษา

พระองค์ทรงช่วยพวกเขาจากหลุมฝังศพ

21ให้พวกเขาขอบพระคุณองค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับความรักมั่นคงของพระองค์

และสำหรับพระราชกิจมหัศจรรย์ของพระองค์ที่ทำเพื่อมนุษย์

22ให้เขาถวายเครื่องบูชาขอบพระคุณ

และบอกเล่าถึงพระราชกิจต่างๆ ของพระองค์ด้วยบทเพลงแห่งความชื่นชมยินดี

23บางคนก็ลงเรือออกไปกลางทะเล

พวกเขาทำมาค้าขายตามเส้นทางมหาสมุทร

24พวกเขาได้เห็นพระราชกิจขององค์พระผู้เป็นเจ้า

เห็นการอัศจรรย์ของพระองค์ในที่ลึก

25เพราะพระองค์ตรัส พายุก็ก่อตัว

ทำให้คลื่นซัดสูง

26พวกเขาถูกโยนขึ้นฟ้าแล้วก็ดิ่งลงมาในห้วงลึก

ขวัญหนีดีฝ่อไปเพราะวินาศภัยรุนแรง

27พวกเขาถลาและซวนเซไปเหมือนคนเมาเหล้า

พวกเขาจนปัญญาไม่รู้จะทำอย่างไร

28แล้วพวกเขาร้องทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าในความทุกข์ยาก

และพระองค์ทรงนำพวกเขาออกจากความทุกข์เข็ญ

29พระองค์ทรงทำให้พายุสงบลงเป็นเพียงเสียงกระซิบ

ทำให้คลื่นในทะเลเงียบสงบ

30พวกเขาดีใจที่ทะเลสงบ

และพระองค์ทรงนำพวกเขาเข้าเทียบท่าดังหมาย

31ให้พวกเขาขอบพระคุณองค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับความรักมั่นคงของพระองค์

และสำหรับพระราชกิจมหัศจรรย์ของพระองค์ที่ทำเพื่อมนุษย์

32ให้พวกเขาเทิดทูนพระองค์ในที่ประชุมประชากร

และสรรเสริญพระองค์ในที่ประชุมผู้อาวุโส

33พระองค์ทรงเปลี่ยนแม่น้ำให้กลายเป็นทะเลทราย

ธารน้ำไหลกลายเป็นผืนดินแตกระแหง

34ทรงเปลี่ยนดินแดนอุดมให้กลายเป็นถิ่นร้างซึ่งดินกร่อย

เพราะความชั่วร้ายของผู้อาศัยที่นั่น

35พระองค์ทรงเปลี่ยนถิ่นกันดารให้กลายเป็นแอ่งน้ำ

และเปลี่ยนแผ่นดินที่แตกระแหงให้กลายเป็นน้ำพุ

36พระองค์ทรงนำคนหิวโหยไปอาศัยที่นั่น

และให้พวกเขาพบเมืองที่พวกเขาจะตั้งถิ่นฐาน

37พวกเขาหว่านในท้องนา เพาะปลูกในสวนองุ่น

และเก็บเกี่ยวพืชพันธุ์ธัญญาหารได้อย่างอุดมสมบูรณ์

38พระองค์ทรงอวยพรและพวกเขาก็ทวีจำนวนขึ้น

และพระองค์ไม่ได้ให้ฝูงสัตว์ของพวกเขาลดจำนวนลง

39แล้วพวกเขาถูกลดจำนวนลงและทำให้ตกต่ำ

จากการกดขี่ข่มเหง ทุกข์ภัย และความเศร้าโศก

40พระองค์ผู้ทรงเทการดูถูกดูแคลนลงเหนือเหล่าเจ้านาย

ได้ทรงทำให้พวกเขาระหกระเหินอยู่ในที่เริศร้างไร้หนทาง

41แต่พระองค์ทรงยกชูผู้ยากไร้ออกจากความทุกข์ลำเค็ญ

และให้มีลูกหลานมากมายอย่าง

ฝูงแพะแกะ

42คนเที่ยงธรรมเห็นแล้วชื่นชมยินดี

แต่คนชั่วร้ายทั้งปวงปิดปากเงียบ

43ผู้ใดฉลาดจงฟังสิ่งเหล่านี้

และใคร่ครวญถึงความรักยิ่งใหญ่ขององค์พระผู้เป็นเจ้า