መዝሙር 105 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 105:1-45

መዝሙር 105

የእስራኤል ድንቅ ታሪክ

105፥1-15 ተጓ ምብ – 1ዜና 16፥8-22

1እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ሥራውንም በሕዝቦች መካከል ግለጡ።

2ተቀኙለት፤ ዘምሩለት፤

ድንቅ ሥራዎቹንም ሁሉ ተናገሩ።

3በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤

እግዚአብሔርን የሚሹት ልባቸው ደስ ይበለው።

4እግዚአብሔርንና ብርታቱን ፈልጉ፤

ፊቱንም ዘወትር ፈልጉ።

5ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች፣

ታምራቱንና ከአፉ የወጣውን ፍርድ አስቡ፤

6እናንተ የአገልጋዩ የአብርሃም ዘሮች፣

ለራሱም የመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፤ አስታውሱ።

7እርሱ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤

ፍርዱም በምድር ሁሉ ላይ ነው።

8ኪዳኑን ለዘላለም፣

ያዘዘውንም ቃል እስከ ሺሕ ትውልድ ያስታውሳል።

9ከአብርሃም ጋር ያደረገውን ኪዳን፣

ለይስሐቅም በመሐላ የተሰጠውን ተስፋ አይረሳም።

10ይህንም ለያዕቆብ ሥርዐት አድርጎ፣

ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን አድርጎ አጸናለት፤

11እንዲህም አለ፤ “የርስትህ ድርሻ አድርጌ፣

የከነዓንን ምድር እሰጥሃለሁ።”

12በቍጥር አነስተኞች ሆነው ሳሉ፣

እጅግ ጥቂትና ባይተዋሮች ሳሉ፣

13ከሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲንከራተቱ፣

ከአንዱ መንግሥት ወደ ሌላው ሲቅበዘበዙ፣

14ማንም ግፍ እንዲፈጽምባቸው አልፈቀደም፤

ስለ እነርሱም ነገሥታትን እንዲህ ሲል ገሠጸ፤

15“የቀባኋቸውን አትንኩ፤

በነቢያቴም ላይ ክፉ አታድርጉ።”

16በምድሪቱ ላይ ራብን ጠራ፤

የምግብንም አቅርቦት ሁሉ አቋረጠ፤

17በባርነት የተሸጠውን ሰው፣

ዮሴፍን ከእነርሱ አስቀድሞ ላከ።

18እግሮቹ በእግር ብረት ተላላጡ፤

በዐንገቱም የብረት ማነቆ ገባ።

19የተናገረው ቃል እስኪፈጸምለት፣

የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው።

20ንጉሥ ልኮ አስፈታው፤

የሕዝቦችም ገዥ ነጻ አወጣው።

21የቤቱ ጌታ፣

የንብረቱም ሁሉ አስተዳዳሪ አደረገው፤

22ይኸውም ሹማምቱን በራሱ መንገድ ይመራ ዘንድ፣

ታላላቆቹንም ጥበብ ያስተምር ዘንድ ነበር።

23እስራኤል ወደ ግብፅ ገባ፤

ያዕቆብ በካም ምድር መጻተኛ ሆነ።

24እግዚአብሔር ሕዝቡን እጅግ አበዛ፤

ከጠላቶቻቸውም ይልቅ አበረታቸው፤

25ሕዝቡን እንዲጠሉ፣

በባሪያዎቹም ላይ እንዲያሤሩ ልባቸውን ለወጠ።

26ባሪያውን ሙሴን፣

የመረጠውንም አሮንን ላከ።

27እነርሱም ታምራታዊ ምልክቶችን በመካከላቸው፣

ድንቅ ነገሮቹንም በካም ምድር አደረጉ።

28ጨለማን ልኮ ምድሪቱን ጽልመት አለበሰ፤

እነርሱም በቃሉ ላይ ማመፅን ተዉ።

29ውሃቸውን ወደ ደም ለወጠ፤

ዓሦቻቸውንም ፈጀ።

30ምድራቸውም፣ የነገሥታታቸው እልፍኝ ሳይቀር፣

ጓጕንቸር ተርመሰመሰባቸው።

31እርሱ በተናገረ ጊዜ የዝንብ መንጋ መጣ፤

ትንኞችም ምድራቸውን ወረሩ።

32ዝናባቸውን በረዶ አደረገው፤

ምድራቸውም ሁሉ መብረቅ አወረደ።

33ወይናቸውንና በለሳቸውን መታ፤

የአገራቸውንም ዛፍ ከተከተ።

34እርሱ በተናገረ ጊዜ አንበጣ መጣ፤

ስፍር ቍጥር የሌለውም ኵብኵባ ከተፍ አለ፤

35የምድሪቱንም ዕፀዋት ሁሉ በላ፤

የመሬታቸውንም ፍሬ ሙጥጥ አደረገ፤

36ደግሞም በአገራቸው ያለውን በኵር ሁሉ፣

የኀይላቸውንም ሁሉ በኵራት መታ።

37የእስራኤልንም ሕዝብ ብርና ወርቅ ጭኖ እንዲወጣ አደረገ፤

ከነገዶቻቸውም አንድም አልተደናቀፈም።

38እጅግ ፈርተዋቸው ነበርና፣

ወጥተው ሲሄዱ ግብፅ ደስ አላት።

39ደመናን እንደ መጋረጃ ዘረጋላቸው፤

እሳትም በሌሊት አበራላቸው።

40በለመኑትም ጊዜ፣ ድርጭት አመጣላቸው፤

የሰማይንም እንጀራ አጠገባቸው።

41ዐለቱን ሰነጠቀ፤ ውሃም ተንዶለደለ፤

እንደ ወንዝም በበረሓ ፈሰሰ።

42ለባሪያው ለአብርሃም የሰጠውን፣

ቅዱስ የተስፋ ቃሉን አስቧልና።

43ሕዝቡን በደስታ፣

ምርጦቹንም በእልልታ አወጣቸው።

44የሌሎችን ሕዝቦች ምድር ሰጣቸው፤

የእነዚህንም የድካም ፍሬ ወረሱ፤

45ይህም ሥርዐቱን ይጠብቁ ዘንድ፣

ሕጉንም ይፈጽሙ ዘንድ ነው።

ሃሌ ሉያ።105፥45 እግዚአብሔር ይመስገን የሚሉ ትርጕሞች አሉ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 105:1-45

第 105 篇

上帝和祂的子民

(平行经文:历代志上16:8-22

1你们要称谢耶和华,呼求祂的名,

在列邦传扬祂的作为。

2要歌颂、赞美祂,

述说祂一切奇妙的作为。

3要以祂的圣名为荣,

愿寻求耶和华的人都欢欣。

4要寻求耶和华和祂的能力,

时常来到祂面前。

5-6祂仆人亚伯拉罕的后裔,

祂所拣选的雅各的子孙啊,

要记住祂所行的神迹奇事和祂口中的判词。

7祂是我们的上帝耶和华,

祂在普天下施行审判。

8祂永远记得祂的约,

历经千代也不忘祂的应许,

9就是祂与亚伯拉罕所立的约,

以撒所起的誓。

10祂把这约定为律例赐给雅各

定为永远的约赐给以色列

11祂说:“我必把迦南赐给你,

作为你的产业。”

12那时他们人丁稀少,

在当地寄居。

13他们在异国他乡流离飘零。

14耶和华不容人压迫他们,

还为他们的缘故责备君王,

15说:“不可难为我膏立的人,

也不可伤害我的先知。”

16祂在那里降下饥荒,

断绝一切食物的供应。

17祂派一个人率先前往,

这人就是被卖为奴隶的约瑟

18他被戴上脚镣,套上枷锁,

19直到后来他的预言应验,

耶和华的话试炼了他。

20埃及王下令释放他,

百姓的首领给他自由,

21派他执掌朝政,

管理国中的一切,

22有权柄管束王的大臣,

将智慧传授王的长老。

23以色列来到埃及

寄居在地。

24耶和华使祂的子民生养众多,

比他们的仇敌还要强盛。

25祂使仇敌憎恨他们,

用诡计虐待他们。

26祂派遣祂的仆人摩西和祂拣选的亚伦

27埃及行神迹,

地行奇事。

28祂降下黑暗,使黑暗笼罩那里;

他们没有违背祂的话。

29祂使埃及的水变成血,

鱼都死去;

30又使国中到处是青蛙,

王宫禁院也不能幸免。

31祂一发命令,

苍蝇蜂拥而至,虱子遍满全境。

32祂使雨变成冰雹,

遍地电光闪闪。

33祂击倒他们的葡萄树和无花果树,

摧毁他们境内的树木。

34祂一发声,

就飞来无数蝗虫和蚂蚱,

35吃尽他们土地上的植物,

吃尽他们田间的出产。

36祂又击杀他们境内所有的长子,

就是他们年轻力壮时生的长子。

37祂带领以色列人携金带银地离开埃及

各支派中无人畏缩。

38埃及人惧怕他们,

乐见他们离去。

39祂铺展云彩为他们遮荫,

晚上用火给他们照明。

40他们祈求,

祂就赐下鹌鹑,降下天粮,

叫他们饱足。

41祂使磐石裂开、涌出水来,

在干旱之地奔流成河。

42因为祂没有忘记祂赐给仆人亚伯拉罕的神圣应许。

43祂带领自己的子民欢然离去,

祂所拣选的百姓欢唱着前行。

44祂把列国的土地赐给他们,

使他们获得别人的劳动成果。

45祂这样做是要使他们持守祂的命令,

遵行祂的律法。

你们要赞美耶和华!