መዝሙር 100
እግዚአብሔርን ለማመስገን የቀረበ ግብዣ
የምስጋና መዝሙር።
1ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር እልል በሉ፤
2እግዚአብሔርን በደስታ አገልግሉት፤
በፍሥሓ ዝማሬ ፊቱ ቅረቡ።
3እግዚአብሔር አምላክ መሆኑን ዕወቁ፤
እርሱ ፈጠረን፤ እኛም የእርሱ ነን፤
እኛ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን።
4በምስጋና ወደ ደጆቹ፣
በውዳሴም ወደ አደባባዮቹ ግቡ፤
አመስግኑት፤ ስሙንም ባርኩ፤
5እግዚአብሔር ቸር፣ ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፤
ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው።