መክብብ 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መክብብ 8:1-17

1ነገሮችን መግለጽ የሚችል፣

እንደ ጠቢብ ያለ ሰው ማን ነው?

ጥበብ የሰውን ፊት ታበራለች፤

የከበደ ገጽታውንም ትለውጣለች።

ንጉሥን ታዘዝ

2በእግዚአብሔር ፊት መሐላ ስለ ፈጸምህ፣ የንጉሥን ትእዛዝ አክብር እልሃለሁ። 3ከንጉሥ ፊት ተጣድፈህ አትውጣ፤ የወደደውንም ማድረግ ስለሚችል ለጥፋት አትሰለፍ። 4የንጉሥ ቃል የበላይ ስለሆነ እርሱን፣ “ምን ታደርጋለህ?” ማን ሊለው ይችላል?

5እርሱን የሚታዘዝ ሁሉ አይጐዳም፤

ጥበበኛም ልብ ትክክለኛውን ጊዜና ተገቢውን አሠራር ያውቃል።

6የሰው መከራ እጅግ ቢጫነውም፣

ለሁሉም ነገር ትክክለኛ ጊዜና ተገቢ አሠራር አለው።

7ሰው የወደ ፊቱን ስለማያውቅ፣

ሊመጣ ያለውን ማን ሊነግረው ይችላል?

8ሰው ነፋስን መቈጣጠር አይችልም8፥8 ወይም መንፈሱን ለማቈየት አይችልም

በዕለተ ሞቱም ላይ ሥልጣን ያለው ማንም የለም፤

በጦርነት ጊዜ ማንም ከግዴታ ነጻ እንደማይሆን፣

ክፋትም የሚለማመዷትን አትለቃቸውም።

9ከፀሓይ በታች የተሠራውን ሁሉ በአእምሮዬ መርምሬ፣ ይህን ሁሉ አየሁ። ሰው ሰውን ለመጕዳት ገዥ የሚሆንበት ጊዜ አለ። 10እንዲሁም ወደ ቅዱሱ ስፍራ ይመጡና ይሄዱ የነበሩት ክፉዎች ተቀብረው አየሁ፤ ይህን ባደረጉበት ከተማም ይመሰገኑ ነበር8፥10 አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆችና ሰብዓ ሊቃናት (አቍዊላ) እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን ተረስተዋል ይላሉ።፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነው።

11በወንጀል ላይ ባፋጣኝ ፍርድ ካልተሰጠ፣ የሰዎች ልብ ክፉን በማድረግ ዕቅድ ይሞላል። 12ኀጥእ መቶ ወንጀል ሠርቶ ዕድሜው ቢረዝምም፣ እግዚአብሔርን የሚያከብሩ፣ ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላቸው ሰዎች መልካም እንደሚሆንላቸው ዐውቃለሁ። 13ነገር ግን ክፉዎች እግዚአብሔርን ስለማይፈሩ መልካም አይሆንላቸውም፤ ዕድሜያቸው እንደ ጥላ አይረዝምም።

14በምድር ላይ የሚከሠት ሌላም ከንቱ ነገር አለ፤ ጻድቃን ለክፉዎች የሚገባውን፣ ክፉ ሰዎችም ለጻድቃን የሚገባውን ይቀበላሉ፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነገር ነው አልሁ። 15ለሰው፣ ከፀሓይ በታች ከመብላት፣ ከመጠጣትና ከመደሰት ሌላ የተሻለ ነገር ስለሌለ፣ በሕይወት ደስ መሰኘት መልካም ነው አልሁ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ከፀሓይ በታች በሰጠው የሕይወት ዘመኑ ሁሉ በሥራው ደስታ ይኖረዋል።

16ጥበብን ለማወቅና ሌት ተቀን እንቅልፍ የማያውቀውን በምድር ያለውን የሰውን ድካም ለመገንዘብ በአእምሮዬ ስመረምር፣ 17እግዚአብሔር ያደረገውን ሁሉ አየሁ። ከፀሓይ በታች የሚደረገውን ማንም ሊያውቅ አይችልም፤ ሰው ለመመርመር ብዙ ቢጥርም፣ ትርጕሙን ማግኘት አይችልም፤ ጠቢብም እንኳ ዐውቀዋለሁ ቢል፣ ፈጽሞ ሊገነዘበው አይችልም።

Thai New Contemporary Bible

ปัญญาจารย์ 8:1-17

1ใครเล่าเสมอเหมือนคนฉลาด?

ใครเล่ารู้คำอธิบายของสิ่งต่างๆ?

สติปัญญาทำให้หน้าตาของคนเราแจ่มใส

และทำให้สีหน้าแข็งกระด้างเปลี่ยนไป

เชื่อฟังกษัตริย์

2จงเชื่อฟังพระบัญชาของกษัตริย์ เพราะท่านได้ปฏิญาณไว้ต่อหน้าพระเจ้าแล้ว 3อย่าหุนหันออกไปให้พ้นพระพักตร์กษัตริย์ อย่ายืนหยัดปกป้องสิ่งที่ไม่ดี เพราะพระองค์จะทรงกระทำสิ่งใดก็ได้ตามแต่ชอบพระทัย 4เนื่องจากพระดำรัสของกษัตริย์มีอำนาจสูงสุด ใครจะแย้งพระองค์ได้ว่า “พระองค์ทรงทำอะไรเช่นนั้น?”

5ผู้ใดเชื่อฟังคำบัญชาของพระองค์จะไม่ประสบอันตราย

จิตใจของคนมีปัญญาจะรู้โอกาสและวิธีการอันเหมาะอันควร

6เพราะมีโอกาสและวิธีการที่เหมาะสมสำหรับทุกสิ่ง

แม้ว่าความทุกข์ยากของมนุษย์จะถาโถมเข้าใส่เขาอย่างหนักหน่วงก็ตาม

7เนื่องจากไม่มีมนุษย์คนใดหยั่งรู้อนาคต

ใครเล่าจะสามารถบอกได้ว่าจะมีอะไรเกิดขึ้น?

8ไม่มีใครฉุดรั้งจิตวิญญาณ8:8 หรือลมไว้ได้ฉันใด

ก็ไม่มีใครมีอำนาจเหนือวันตายฉันนั้น

ยามสงครามไม่มีการปลดประจำการฉันใด

ความชั่วร้ายก็จะไม่ยอมปล่อยคนชั่วฉันนั้น

9ข้าพเจ้าเห็นมาหมดแล้ว เมื่อใส่ใจกับทุกสิ่งที่ทำกันภายใต้ดวงอาทิตย์ ก็พบว่าบางครั้งมีคนขึ้นมามีอำนาจเหนือผู้อื่น แต่กลับเป็นภัยแก่ตน8:9 หรือพวกเขา 10และข้าพเจ้าก็เห็นบรรดาคนชั่วร้ายถูกฝัง ผู้ซึ่งเข้าออกในสถานบริสุทธิ์และได้รับการยกย่อง8:10 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูส่วนใหญ่ว่าและถูกลืมในนครซึ่งเขาทำชั่วนั่นแหละ นี่ก็อนิจจัง

11เมื่ออาชญากรยังไม่ได้ถูกตัดสินลงโทษ จิตใจของผู้คนก็เต็มไปด้วยกลอุบายที่จะทำผิด 12ถึงแม้คนชั่วจะก่อกรรมทำเข็ญเป็นร้อยครั้งและยังมีชีวิตอยู่ยืนยาว ข้าพเจ้าก็ยังรู้แน่แก่ใจว่าบรรดาผู้ที่ยำเกรงพระเจ้าซึ่งอยู่ต่อหน้าพระองค์ย่อมได้ดีกว่า 13เนื่องจากคนชั่วไม่ยำเกรงพระเจ้า เขาจะไม่ได้ดีและวันคืนของเขาจะไม่ทอดยาวเหมือนเงา

14มีสิ่งอนิจจังอีกอย่างที่เกิดขึ้นในโลกนี้คือ คนชอบธรรมรับผลที่ควรตกแก่คนชั่ว แต่คนชั่วกลับรับผลที่ควรตกแก่คนชอบธรรม ข้าพเจ้ากล่าวว่า นี่ก็อนิจจัง 15ฉะนั้นข้าพเจ้าจึงสนับสนุนให้ชื่นชมกับชีวิต เพราะสำหรับมนุษย์ที่อยู่ภายใต้ดวงอาทิตย์แล้ว ไม่มีอะไรดีไปกว่ากินดื่มและเปรมปรีดิ์ แล้วความชื่นชมยินดีจะอยู่เคียงข้างเขาไปในการงาน ตลอดวันคืนแห่งชีวิตซึ่งพระเจ้าประทานแก่เขาภายใต้ดวงอาทิตย์

16เมื่อข้าพเจ้าใส่ใจที่จะรู้จักสติปัญญา และสังเกตการตรากตรำทำงานของผู้คนในโลกนี้ พวกเขาอดนอนทั้งวันทั้งคืน 17แล้วข้าพเจ้าก็เห็นทุกสิ่งที่พระเจ้าทรงทำ ไม่มีใครเข้าใจสิ่งที่เป็นไปภายใต้ดวงอาทิตย์ แม้จะทุ่มเทแรงกายแรงใจทั้งหมด แสวงหาคำตอบ แต่มนุษย์ก็ไม่พบความหมาย ต่อให้คนฉลาดซึ่งอ้างว่าตนรู้ก็ไม่ได้เข้าใจอย่างถ่องแท้